1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

በቤንሻንጉል ያላባራው የሰላማዊ ዜጎች ጥቃት 

ሰኞ፣ ታኅሣሥ 5 2013

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የመተከልን ዞን ቡለንና ድባጢ ወረዳ ነዋሪዎች ታጣቂዎች በተደጋጋሚ ጥቃት እያደረሱባቸው መሆኑን አመለከቱ። ከባለፈው ረቡዕ አንስቶ በቡለን ወረዳ  ሁለት ቀበሌዎች ውስጥ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት አምስት የሚደርሱ ሰዎች ሕይወት ማለፉን ተናግረዋል።

Äthiopien Benishangul Region, Stadt  Metekel
ምስል፦ Negassa Dessakegen/DW

«ተጠርጣሪዎች መያዛቸው ተነግሯል»

This browser does not support the audio element.

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የመተከልን ዞን ቡለንና ድባጢ ወረዳ ነዋሪዎች ታጣቂዎች በተደጋጋሚ ጥቃት እያደረሱባቸው መሆኑን አመለከቱ። በክልሉ የመተከል ዞን የአስቸኳይ ጊዜ አስተዳደር /ኮማንድ ፖስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ በበኩሉ ከ1000 የሚበልጡ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳዩቸው እየታየ እንደሚገኝ ትናንት በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ገልጿል። ከዚህ በተጨማሪም በየደረጃው ያሉ አመራሮችን እና የፖሊስ አባላት ላይ ጭምር ኃላፊነታቸውን በአግባቡ አልተወጡም ባላቸው ላይ እርምጃ መውሰዱን አመልክቷል። ሕግን ለማስከበር በሚያደርገው ጥረትም 277 ዘመናዊና ባህላዊ የጦር መሣሪያዎችን እንዲሁም የወታደር አልባሳቶችንም በቁጥጥር ስር ማዋሉን ጠቁሟል። ከባለፈው ረቡዕ አንስቶ በቡለን ወረዳ  ሁለት ቀበሌዎች ውስጥ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት አምስት የሚደርሱ ሰዎች ሕይወት ማለፉን ተናግረዋል። በተለያዩ ጊዜያ ታጣቂዎች በሰው እና በንብረት ላይ ጉዳት ማድረሳቸውን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።

ነጋሳ ደሳለኝ

ሸዋዬ ለገሠ

እሸቴ በቀለ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW