1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

በትግራይ ክልል ኃይሎችና በቀድሞ አባላቱ መካከል የተካሄደ ግጭት

ሚሊዮን ኃይለ-ሥላሴ
ሰኞ፣ ነሐሴ 5 2017

በተጋሩ መካከል የእርስ በርስ ግጭት እንዳይከሰት ጥረት እያደረገ እንዳለ የሚገልፀው የትግራይ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ፥ በስም ያልጠራቸው ይሁንና 'ወዶገብ፣ ነጭ ለባሽ' በሚሉ እና ሌሎች አገላለፃች ያስቀመጣቸው አካላት ተጋሩን እርስበርስ ለማዋጋት ፕሮጀክት በመያዝ አፋር ያሉ ታጣቂዎችን ተጠቅመው በትግራይ ኃይሎች ላይ ጥቃት ሰንዝረዋል ብሏል።

Amanual Asefa - Vizepräsident der Interimsverwaltung
ምስል፦ Milion Hailesillassie/DW

በትግራይ ኃይሎችና በቀድሞ አባላቱ መካከል የተካሄደ ግጭት

This browser does not support the audio element.


የትግራይ ክልል ኃይሎች ከፍተኛ አዛዦች ለአንድ የህወሓት ቡድን ያጋደለ ውሳኔ አስተላለፉ በማለት የተለየ ፖለቲካዊ አመለካከት በመያዝ እንዲሁም ከዋናው ኃይል በመለየት በአፋር ክልል ሲደራጁ የቆዩ ታጣቂዎች ከቅርብ ግዜ ወዲህ ወደ ትግራይ ዘልቀው በመግባት ጥቃቶች እየሰነዘሩ ነው በማለት የትግራይ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ባወጣው መግለጫ ከሷል።

ቢሮው ባወጣው መግለጫ ማዕከላቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ፣ ቤተሰቦቻቸውን ውጭ ሀገር አስቀምጠው የትግራይን ወጣት ለአመፅ እየጠሩ ነው ሲል ወቅሷል። በተጋሩ መካከል የእርስ በርስ ግጭት እንዳይከሰት ጥረት እያደረገ እንዳለ የሚገልፀው የትግራይ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ፥ ይሁንና እነዚህ በስም ያልጠራቸው ይሁንና 'ወዶገብ፣ ነጭ ለባሽ' በሚሉ እና ሌሎች አገላለፃች ያስቀመጣቸው አካላት ተጋሩን እርስበርስ ለማዋጋት ፕሮጀክት በመያዝ አፋር ያሉ ታጣቂዎችን ተጠቅመውበትግራይ ኃይሎች ላይ ጥቃት ሰንዝረዋል ብሏል። ይህ ጥቃት ለሁለተኛ ግዜ የተሰነዘረ ነው ያለው ይህ መግለጫ፥ በዚህም ለሁለተኛ ጊዜ የአንድ አባላቸው ህይወት ማለፉን አመልክቷል። ይህን ባደረጉት ላይም አስተማሪ እርምጃ እንደሚወስድ ዝቷል። 

በእነዚህ ኃይሎች መካከል እየታዩ ያሉ ግጭቶች እንዲሁም ወቅታዊ የህወሓት እና የፌደራል መንግስት አለመግባባቶች በትግራይ፣ ህዝቡ ዘንድ ስጋት ፈጥሮ ይገኛል። ትናንት በነበረ መድረክ የተናገሩት የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዝደንት አቶ አማኑኤል አሰፋ፥ የትግራይ ህዝብ ፍላጎት ሰላም ነው ሲሉ ተናግረው። ከኢትዮጵያ መንግስት የፕሪቶርያ ስምምነት ይዘቶችን በሙሉእነት መፈፀም እንደሚጠበቅ የተናገሩት አቶ አማኑኤል ከዚህ በተፃራሪ፥ ይህ ሲባል ትግራይን በጦርነት ዝግጅት መወንጀል አይገባም ሲሉ አክለዋል።

አቶ አማኑኤል "የትግራይ ጥያቄዎች መሰረታዊ ነገሮች ናቸው። የትግራይ ህዝብ ሉአላዊነቱ ተወሮ፣ ከቆዬ ተፈናቅሎ፣ ማሕበረ ኢኮኖሚያዊ ወድሞ፣ ሰላም አጥቶ፣ የነበረው አጥቶ እና ተክዶ ነው ያለው። አሁንም እየጠየቀ ያለው ወደነበረበት ሁኔታ እንዲመለስ ነው" ብለዋል።
በፌደራሉ መንግስት እና ህወሓት መካከል ያለው መካረር ለመፍታት የሃይማኖት መሪዎች እና ሀገር ሽማግሌዎች ጥረት ላይ መሆናቸው በቅርቡ ሲገልፁ ነበር።

ሚሊዮን ኃይለ ሥላሴ 
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ 
 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW