1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

በትግራይ ክልልና በአካባቢዉ ያንዣበበዉ የጦርነት ሥጋት

ነጋሽ መሐመድ
ዓርብ፣ ጥቅምት 28 2018

የአፋር ክልል መስተዳድር ባለፈዉ ሮብ ባወጣዉ መግለጫ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጭምር አደረሱት ያለዉን ጥቃት አጥብቆ አዉግዟል።የትግራይ ክልል ተቃዋሚ ፓርቲ ዴሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ ዛሬ ባወጣዉ መግለጫ ደግሞ «አጥፎ ጠፊ» ያለዉ የትግራይ ክልል ገዢ ፓርቲ ህወሓት፣ ከኤርትራዉ ሻዕቢያ ጋር በመሆን ጦርነት አዉጀዋል ብሏል

የአፋር ክልላዊ መስተዳድርና የትግራይ ተቃዋሚ ፓርቲ ዴሞክራሲያዊ ስምረት እንዳስታወቁት የትግራይ ታጣቂዎች አፋር ክልልና እዚያዉ ትግራይ ዉስጥ የተለያዩ አካባቢዎችን አጥቅተዋል
የትግራይ መከላከያ ኃይል (TDF-በእንግሊዝኛ ምሕፃሩ) ተብሎ የሚጠራዉ የትግራይ ክልል ወታደራዊ ኃይል ባልደረቦች የሰልፍ treዒት ሲያሳዩ።መቀሌ፣ ጥቅምት 2018ምስል፦ Million Haileslassie/DW

በትግራይ ክልልና በአካባቢዉ ያንዣበበዉ የጦርነት ሥጋት

This browser does not support the audio element.

የትግራይ ክልል ታጣቂዎች የክልሉን ድንበር ተሻግረዉ አፋር ክልል፣ ዞን ሁለት ዉስጥ 6 ቀበሌዎችን አጥቅተዋል መባሉ ወትሮም ዉጥረት የተጫጫነዉን አካባቢ ከዳግም ጦርነት እንዳይከተዉ አስግቷል።የአፋር ክልል መስተዳድርባለፈዉ ሮብ (ጥቅምት 26) ባወጣዉ መግለጫ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጭምር አደረሱት ያለዉን ጥቃት አጥብቆ አዉግዟል።የትግራይ ክልል ተቃዋሚ ፓርቲ ዴሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ ዛሬ ባወጣዉ መግለጫ ደግሞ «አጥፎ ጠፊ» ያለዉ የትግራይ ክልል ገዢ ፓርቲ ህወሓት፣ ከኤርትራዉ ሻዕቢያ ጋር በመሆን ጦርነት አዉጀዋል ብሏል።

የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ግን ተፈፀመ የተባለዉን ጥቃት አስተባብሏል።ማሕበራዊ መገናኛ ዘዴዎች እንደዘገቡት ደግሞ የኢትዮጵያ የመከላከያ ጦር ትግራይ ዉስጥ የሚገኝ የጦር መሳሪያ ማከማቻ መጋዘንን በሰዉ አልባ አዉሮፕላን ደብድቧል።ደረሱ የተባሉት ጥቃቶች፣ የቃላት ዉግዘትና አፀፋ ዉግዘቱን በተመለከተ ዩሐንስ ገብረ እግዚአብሄርን አነጋግሬዋለሁ።

ነጋሽ መሐመድ

እሸቴ በቀለ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW