በኖርዌይ የኢትዮጵያውያን ስደተኞች ችግር19 ነሐሴ 2003ሐሙስ፣ ነሐሴ 19 2003በኖርዌይ ለበርካታ ዓመታት ነዋሪ እንደሆኑ የገለፁ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች «አሁንም ችግራችን አልተፈታም፣ ሆኖም ግን ወደ ሀገራችን እንድንመለስ ግፊት እየተደረገብን ነው» ሲሉ ለዶቼ ቬሌ ገልፀዋል። እንደ ስደተኞቹ ገለፃ ከሆነ በኖርዌይ ከ 17 ዓመታት በላይ የኖሩ፣ ቤት ንብረት እና ቤተሰብ እዛው ኖርዌይ ውስጥ ያፈሩማገናኛዉን ኮፒ አድርግኖርዌይ፥ መልከዓ-ምድርማስታወቂያኢትዮጵያውያን ችግሩ ደርሶባቸዋል። ኢትዮጵያውያን ስደተኞቹ ለሚመለከታቸው የኖርዌይ መንግስት አካላት በተደጋጋሚ ያሰሙት አቤቱታ ተቀባይነት ባለማግኘቱ ተቃውሞዋቸውን በእግር ጉዞ ገልፀዋል። ከተጓዦቹ መካከል ስደተኞቹን በማስተባበር የኮሚቴ አባል የሆነው ፍቅሬ ዘለቀው የኢትዮጵያውያኑን ብሶት ያብራራል። ማንተጋፍቶት ስለሺ ነጋሽ መሐመድ