1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

በተያዘው አመት ከትግራይ 18 ሺሕ ገደማ ወጣቶች በሕገ-ወጥ መንገድ ስደት ገብተዋል

ማክሰኞ፣ ሐምሌ 30 2011

ከትግራይ ክልል ባለፈው አንድ አመት ብቻ 18 ሺሕ ገደማ ወጣቶች በሕገ-ወጥ መንገድ ስደት መግባታቸውን የክልሉ ሰራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ። ባለፈው ሐምሌ 18 ቀን ሜድትራኒያን ባሕር ላይ በደረሰ የጀልባ መስጠም አደጋ ከሞቱ ስደተኞች መካከል 16ቱ ከትግራይ ክልል ኢሮብ ወረዳ የተነሱ መሆናቸው ታውቋል።

Libysche Migranten ertrunken
ምስል፦ picture-alliance/AP Photo/H. Ahmed

ሜድትራኒያን ከሞቱ ስደተኞች 16ቱ ከኢሮብ ወረዳ የተጓዙ ናቸው

This browser does not support the audio element.

ከትግራይ ክልል ባለፈው አንድ አመት ብቻ 18 ሺሕ ገደማ ወጣቶች በሕገ-ወጥ መንገድ ስደት መግባታቸውን የክልሉ ሰራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ። ሥራ አጥነት፣ የተሳሳተ መረጃ እና የሕገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ግፊት ዋንኛ ገፊ ምክንያት መሆናቸው ተገልጿል። ባለፈው ሐምሌ 18 ቀን ሜድትራኒያን ባሕር ላይ በደረሰ የጀልባ መስጠም አደጋ ከሞቱ ስደተኞች መካከል 16ቱ ከትግራይ ክልል ኢሮብ ወረዳ የተነሱ መሆናቸው ታውቋል። የሟች ቤተሰቦች ሐዘን ተቀምጠዋል። ከሁለት ሳምንት ገደማ በፊት በደረሰው አደጋ ወደ 150 ገደማ ሰዎች ሳያልቁ እንዳልቀረ ይገመታል።  
ሚሊዮን ኃይለስላሴ 
ኂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW