1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በአማራ ክልል በያዝነው ወር በተከሰተ የመሬት ናዳ በሶስት ወረዳዎች 19 ሰዎች ሞቱ

እሑድ፣ ነሐሴ 19 2016

በአማራ ክልል የትናንትናውን ጨምሮ በያዝነው ወር በተከሰተ ናዳ 3 ወረዳዎች በደረሰ የመሬት ናዳ 19 ሰዎች መሞታቸውንና በእንስሳትና በሰብል ላይ ጉዳት መድረሱን የሰሜን ጎንደር ዞን አስተዳደር አስታወቀ፡፡ በስጋት ቀጠና ውስጥ ያሉ ነዋሪዎችን ወደተሻለ አካባቢ ለማስፈር እየተሰራ እንደሆነም አስተዳደሩ አመልክቷል፡

የመሬት ናዳ
ከባድ ዝናብ ባስከተለው ናዳ በሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ የ10 ሰዎች ህይወት አለፈምስል North Gondar zone Disaster Prevention department

በአማራ ክልል በመሬት ናዳ የሰው ህይወት አለፈ

This browser does not support the audio element.

ባለፈው ዓርብ ለቅዳሜ አጥቢያ የክረምቱን ዝናብ ተከትሎ የጣለ ከባድ ዝናብ ባስከተለው ናዳ በሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ የ10 ሰዎች ህይወት ማለፉን የሰሜን ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የዞኑ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ቢምረው ካሳ ዛሬ ለዶይቼ ቬሌ በስልክ ተናግረዋል፡፡ ከ200 በላይ እንስሳት በናዳው መሞታቸውን አቶ ቢምረው ገልፀዋል፡፡
የሰሜን ጎንደር ዞን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሰላምይሁን ሙላት በበኩላቸው በናዳው ህይወታቸው ካለፈው ወገኖች በተጨማሪ 8 ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸው በህክምና ጣቢያዎች ህክምና እየተደረገላቸው ነው ብለዋል፡፡ በዚህ የተፈጥሮ አደጋ 2700 ሰዎች የተፈናቀሉ ሲሆን በ1700 ሄክታር ማሳ ላይ የተዘራ ሰብልም መውደሙን አስረድተዋል፡፡
የዙኑ ምክትል አስተዳዳሪና የንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊው አቶ ቢምረው እንዳሉት የትናንትናውን ጨምሮ በያዝነው ወር በተከሰተ ናዳ በጠለምት፣ በበየዳና አዲአርቃ ወረዳዎች 19 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል፡፡
የተፈናቀሉ ወገኖችንና ስጋት ያለባቸውን አካላት ወደ ደረቃማ ቦታ ለማስፈር ግብረ ኃይል ተቋቁሞ እየተሰራ መሆኑን አቶ ቢምረው ተናግረዋል፡፡
በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የትንበያ እና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ምርምር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አሳምነው ተሾመ የአማራ ክልልን ጨምሮ ብዙ የሀገሪቱ አካባቢዎች  በሚቀጥሉት 10 ቀናት ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው ለዶቼ ቬለ ሰሞኑን አመልክተዋል፡፡ ተቋማቸው ክረምት ዋነኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑ አካባቢዎች "ከመደበኛ በላይ የሆነ የዝናብ ስርጭት" ይኖራል ሲል ትንበያ ማስቀመጡንም አብራርተዋል።

ዓለምነው መኮንን
ልደት አበበ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW