የአማራ ክልል ተፈናቃዮች
ረቡዕ፣ ጥር 29 2011ማስታወቂያ
በአማራ ክልል የተፈናቃዮች ቁጥር ከ2 ወር ባነሰ ጊዜ ውስጥ በእጥፍ እንደጨመረ የክልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበያ ጽ/ቤት መረጃ ይጠቁማል። የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ባለፈው ታኃሣስ ወር አጋማሸ ላይ የአማራ ክልል ተፈናቃዮች ቁጥር 32 ሺህ እንደነበር በወቅቱ በሰጠው መግለጫ አመልክቶ ነበር፡፡ በተለያዩ አካባቢዎች በተፈጠሩ ግጭቶች በአንድ ወር ተኩል ውስጥ ይህ ቁጥር ወደ 62 ማድጉን የክልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አማረ ክንዴ ለDW ተናግረዋል። ያነጋገራቸው የባህርዳሩ ወኪላችን አለምነው መኮንን ቀጣዩን ዘገባ ልኮልናል።
ዓለምነው መኮንን
ማንተጋፍቶት ስለሺ
ኂሩት መለሰ