በአማራ ክልል የንግድ ተቋማት መዘጋት አድማ
ሰኞ፣ የካቲት 12 2010ማስታወቂያ
በአማራ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች የሚኖሩ ምንጮቻችን እንደጠቀሱት ዛሬ የሕዝብ ማመላለሻ ትራንስፖርቶች የንግድ ተቋማት ተዘግተዉ ነዉ የዋሉት በወሎ መርሳ የሚገኙ የዶቼ ቬለ ተከታታይ በስልክ እንደገለፁልን ፌደራል ሕዝቡ እንዲወጣ እያስገደደ ነበር።
አድማዉ የተጠራዉ በኢትዮጵያ ዳግመኛ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከመታወጁ በፊት በኦሮምያ ክልል የተካሄደን ተቃዎሞ ተከትሎ በአማራ ክልል የሚታየዉን የድንበር ጥያቄ ፍትኃዊ የሃብት ክፍፍልን በተመለከተ የተጠራ የተቋሞ መረሐ ግብር ነዉ ሲሉ በጎንደር ከተማ ነዋሪ የሆኑ የዶይቸቬለ ተከታታይ ገልፀዉልናል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የወልቃይት ማንነት አስተባባሪዎች መካከል ኮሎኔል ደመቀ ዘዉዱ እና ሌሎች 10 የፖለቲካ እስረኞች ዛሬ ከእስር መለቀቃቸዉም ታዉቋል። ዛሬ ከወገራና ከዋልድባ በሽብር ክስ እስር ላይ ከነበሩ 35 ታሳሪዎች መካከል የ 32 መቋረጡን የዶይቼ ቬለ ምንጮች ገልፀዋል። ከነዚህ መካከል መነኮሳት እንደሚገኙበት ነዉ የተነገረዉ።
አዜብ ታደሰ
ኂሩት መለሰ