በአሜሪካው የአፍሪካ ቀንድ መልእክተኛ ጉብኝት የመንግሥት አስተያየት
ሰኞ፣ ነሐሴ 10 2013ማስታወቂያ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ጄፍሪ ፌልትማን፤ ለሦስተኛ ዙር የአፍሪካ ቀንድ ጉብኝት ጅቡቲ ገብተዋል። ወደ ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ የሚሄዱት አምባሳደር ፌልትማን ከኢትዮጵያ እና ጅቡቲ በተጨማሪ በዘጠኝ ቀናት ጉብኝታቸው ወደ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችም ጎራ ይላሉ። በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ ለዘጠኝ ወራት የዘለቀው የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት እልባት በሚያገኝበት ሁኔታ ላይ መምከር ዐቢይ ትኩረታቸው የሆነው መልእክተኛው በኢትዮጵያ ተቀናቃኝ ኃይሎች «ወደ ድርድር ጠረጴዛ በአስቸኳይ እንዲመጡ» ነው ጥሪያቸው። በኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ግን ይህን ጥሪ መቀበል ቀላል የሆነ አይመስልም። የገዢው ብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ ባለስልጣን እና በሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ዶ/ር ቢቂላ ሁሪሳ በተለይም ለዶይቼ ቬለ ጥያቄውን መቀበል አስቸጋሪ ነው ብለዋል።
ስዩም ጌቱ
ሸዋዬ ለገሠ
አዜብ ታደሰ