በአርባምንጭ መምህራን አድማ መቱ
ማክሰኞ፣ ጥቅምት 27 2011![Karte Äthiopien englisch](https://static.dw.com/image/6473754_800.webp)
ማስታወቂያ
በአርባምጭ ከተማ አስተዳደር የሚገኙ መምህራን ከባለፈው ሳምንት መጀመሪያ አንስቶ የሥራ ማቆም እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ መምህራኑ ወደ ሥራ ማቆም አድማ የገቡት ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ላዋጡት ገንዘብ ፤ የቦንድ ሰነድም ሆነ የተመላሽ ክፍያ አንዲፈጸምላቸው ያቀረቡት ጥያቄ ምላሽ ባለማግኘቱ ነው ተብሏል። በሥራ ማቆም አድማው ምክንያት በአርባ ምንጭ ከተማ የሚገኙ 10 ትምህርት ቤቶች ካለፈው ሳምንት እስከ ዛሬ ድረስ የመማር ማስተማር ስራቸውን አቋርጠዋል፡፡ በጉዳዩ ላይ የመምህራን ማህበር ተወካዮችን እና የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር የሥራ ሃላፊዎችን ያነጋገረው የሀዋሳው ወኪላችን ዘገባ አድርሶናል፡፡
ሸዋንግዛዉ ወጋየሁ
አዜብ ታደሰ
ተስፋለም ወልደየስ