1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

በአዉሮጳ ኅብረት ተቃዉሞ የገጠመዉ የአሜሪካ የ 28 ነጥብ የሰላም እቅድ

ገበያው ንጉሤ
ሰኞ፣ ኅዳር 15 2018

ዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ ሩስያ በዩክሬን የምታካሂደዉን ጦርነት ለማስቆም ያወጣችዉን ባለ 28 ነጥብ የሰላም እቅድ የአዉሮጳ ኅብረት ተቃወመዉ። ኅብረቱ የራሱ ያለዉን የሰላም አማራጮች ይፋ አድርጓል። ዩናይትድ ስቴትስ ከዩክሬይን ይልቅ ከሞስኮ ጋር የበለጠ ወዳጅነት እንዳላትም ይነገራሉ።

ጄኔቭ የዩኤስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ከዩክሬን ልዑካን ጋር -የሰላም ድርድር 23.11.2025
ጄኔቭ የዩኤስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ከዩክሬን ልዑካን ጋር -የሰላም ድርድር 23.11.2025ምስል፦ Fabrice Coffrini/AFP/Getty Images

በአዉሮጳ ኅብረትና ዩክሬን ተቃዉሞ የገጠመዉ የአሜሪካ የ 28 ነጥብ የሰላም እቅድ 


ዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ ሩስያ በዩክሬንየምታካሂደዉን ጦርነት ለማስቆም ያወጣችዉን ባለ 28 ነጥብ የሰላም እቅድ የአዉሮጳ ኅብረት ተቃወመዉ። ኅብረቱ የራሱ ያለዉዉን የሰላም አማራጮች ይፋ አድርጓል። በአውሮጳ ውስጥ የሚገኙ ፖለቲከኞች እና ተንታኞች የዩናይትድ ስቴትስ ለዩክሪን ሰላም ያመጣል ስትል የሰላም እቅድ ስታዘጋጅ ከአውሮጳ ህብረት እና ከዩክሬን ጋር ሳትመካከር ነዉ ብለዉ ያምናሉ። ዩናይትድ ስቴትስ ከዩክሬይን ይልቅ ከሞስኮ ጋር የበለጠ  ወዳጅነት እንዳላትም ይነገራሉ። 
በአውሮጳ ኅብረት እና በዩናይትድ ስቴትስ መካከል የተነሱት የሰላም እቅዶች፣ ልዩነቶች እና ውዝግቦች ምንድን ናቸዉ? የአዉሮጳ ኅብረት መቀመጫ ብረስልስ ላይ የሚገኘዉን የዶቼ ቬለ ዘጋቢ ገበያዉ ንጉሴን አነጋግረናል። በሌላ በኩል 7ኛው የአውሮጳ ህብረት እና የአፍሪቃ ህብረት የሁለት ቀናት የመሪዎች ጉባኤ ዛሬ አንጎላ መዲና ሉዋንዳ ላይ ዛሬ ጀምሯል። ይህ ሁለቱ አህጉራት የጋራ ጉባኤ በመክፈቻዉ የአውሮጳ ህብረት እና የአፍሪቃ ህብረት አጋርነት 25ኛ ዓመትን አክብሯል። 


ገበያዉ ንጉሴ / አዜብ ታደሰ 
ነጋሽ መሐመድ 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW