1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በአዲስ አበባ እና ኦሮሚያ አዋሳኝ የሰዎች ህይወት ያለፈበት ግጭት

ዓርብ፣ ጥር 13 2014

የወይብላ ማሪያም ታቦታትን ወደ መንበር የሚመልሱ ምዕመናን እና የፀጥታ ኃይሎች መኃል ትናንት በተፈጠረው ግጭት የ2 ሰዎች ህይወት ወዲያውኑ ሲያልፍ በርካቶች መጎዳታቸውን የዓይን እማኞች ለዶይቼ ቬለ ተናገሩ።ታቦታቱን ከጥምቀተ ባህር ወደ መንበር የመመለስ ሂደት ዛሬ ከፍተኛ የጸጥታ ኃይሎች እና የእምነቱ ተከታይ ምዕመናን በተገኙበት ተፈጽሟል፡፡

Äthiopien | Weybla Mariam Kirche in Addis Ababa
ምስል Seyoum Getu/DW

የሁለት ሰዎች ህይወት ያለፈበት ግጭት

This browser does not support the audio element.

ትናንት በአዲስ አበባ ኮልፌ ቀራኒዮ እና ኦሮሚያ ክልል ቡራዩ ከተማ አዋሳኝ አካባቢ የጥምቀት በዓል አክብረው ታቦታት ወደ መንበር የሚመልሱ ምዕመናን እና የፀጥታ ኃይሎች መኃል በተፈጠረው ግጭት የሁለት ሰዎች ህይወት ወዲያውኑ ሲያልፍ በርካቶች መጎዳታቸውን የአይን እማኞች ለዶይቼ ቬለ ተናገሩ። የሟቾቹ ቁጥር ዛሬ ሶስት መድረሱን የሚገልጹት የአይን እማኞች ምናልባትም ክፉኛ የተጎዱ ሰዎች ቁጥር ከፍተኛ በመሆኑ የሟቾች ቁጥሩ ከዚህም ሊጨምር ይችላል ይላሉ። በትናንትናው እለት በፀጥታ ችግር የተስተጓጎለው የወይብላ ማሪያም ታቦታትን ከጥምቀተ ባህር ወደ መንበር የመመለስ ሂደት ዛሬ ከፍተኛ የጸጥታ ኃይሎች እና የእምነቱ ተከታይ ምዕመናን በተገኙበት ተፈጽሟል፡፡ዘጋቢያችን ስዩም ጌቱ የዛሬውንና የትናንቱን ሁነት ተከታትሎ ቀጣዩን ዘገባ አጠናቅሯል።
ስዩም ጌቱ
ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW