1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በአዲስ አበባ የኦሮምያ ልዩ ጥቅሞችን የተመለከተ ረቂቅ አዋጅ

ማክሰኞ፣ ሰኔ 20 2009

የኦሮሚያ ክልል በአዲስ አበባ ከተማ ላይ ያለውን ህገ-መንግሥታዊ ልዩ ጥቅም አስመልክቶ የተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ዝርዝር ይዘት ይፋ ሆነ። የኦሮሚያ ክልል ልዩ ጥቅምን ለማስጠበቅ የወጣውን ረቂቅ አዋጅ በማጸደቅ ሂደት ላይ በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎች ይሳተፉበታል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተዘግቦአል።

Äthiopien - Addis Abeba - City Churchill Road
ምስል DW/Y. Geberegziabehr

Q&A_spiacla Report über Oromia special interest - MP3-Stereo

This browser does not support the audio element.

የኢትዮጵያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የኦሮምያ ክልል በአዲስ አበባ ከተማ የሚኖረውን ልዩ ጥቅምን በተመለከተ የተሰናዳውን ረቂቅ አዋጅ ዛሬ ለኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስተላለፈ። የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሀን እንደዘገቡት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ረቂቅ አዋጁ በኢትዮጵያ ህገ መንግሥት አንቀፅ 49 ንኡስ አንቀጽ 5 የተቀመጡትን ከአገልግሎት አቅርቦት ከተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም እና ከአካባቢ ጥበቃ ጋር የተያያዙ ልዩ ጥቅሞች ያላቸውን ማካተቱን አስታውቋል። በረቂቅ ህጉ አዲስ አበባ እና ኦሮምያን ያስተሳስራሉ አስተዳደራዊ ጉዳዮችን ማዕከል በማድረግ የኦሮምያ ክልልን ልዩ ጥቅም ለማስጠበቅ ያስችላሉ የተባሉ አንቀጾች መካተታቸውም ተዘግቧል። የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ስለ ረቂቅ አዋጁ ምንነት ባጭሩ ገልጿል።

 

ዮሃንስ ገብረእግዚአብሔር

አዜብ ታደሰ 

ኂሩት መለሰ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW