በኢትዮጵያ ነፃ የጋዜጠኞች ምክር ቤት ምሥረታ ጥያቄ
ሰኞ፣ ሰኔ 16 2006ማስታወቂያ
ኢትዮጵያ ውስጥ ከመንግሥትም ከተቃዋሚዎች ነፃ የሆነ የጋዜጠኞች ምክር ቤት እንዲቋቋም ተጠየቀ ። የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ ትናንት አዲስ አበባ ውስጥ የፕሬስ ነፃነትና የጋዜጠኞች ደህንነትና ልማት በሚል ርዕስ በካሄደው ውይይት ላይ የተገኙ ተሳታፊዎች የጋዜጠኝነትን ሙያ የሚያስከብሩ ነፃ ጋዜጠኞች የሚመሩት ማህበር መቋቋም ለሙያው እድገትም ሆነ ለጋዜጠኞች ደህንነት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል ። ጋዜጠኞች በሚታሰሩባት በኢትዮጵያ በፍራቻ ምክንያት ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩሩ ጋዜጦች ቁጥር እያነሰ በመሄድ ላይ መሆኑንም ተሳታፊዎቹ ተናግረዋል ። ውይይቱን የተከታተለው የአዲስ አበባው ወኪላች ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ተከታዩን ዘገባ አጠናቅሯል ።
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ሂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ