1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የእስረኞች መፈታት

ቅዳሜ፣ ጳጉሜን 5 2008

በእነ አቡበከር አህመድ እና በእነ ኤሊያስ ከድር መዝገብ በጸረ-ሽብር ሕግ ተከሰው ተፈርዶባቸው ከነበሩት የሙስሊም መፍትኄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ውስጥ 13ቱ ዛሬ ከእስር ቤት «በይቅርታ» መለቀቃቸው ተገለጠ።

Äthiopien Journalisten Martin Schibbye und Johan Persson
ምስል AP

[No title]

This browser does not support the audio element.

ከሙስሊም መፍትኄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት መካከል 13ቱ እስረኞች ሲፈቱ፤ ከእነ አቡበከር ጋር የታሠሩ አራት እስረኞች ግን አሁንም በእርስ ቤት እንደሚገኙ የእስረኞቹ ጠበቃ አዲስ መሐመድ ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል። ጠበቃዋ፦ አቡበከር አህመድ፣ በድሩ ሑሴን፣ ካሚል ሸምሱ፣ ሙባረክ አደም፣ ሼህ መከተ ሙሔ፣ ኑሩ ቱርኪ፣ ሙራድ ሽኩር፣ ይሱፍ ጌታቸው ከቤተሰባቸው ጋር መቀላቀላቸውን ለዶይቼ ቬለ አረጋግጠዋል። ከዚህ በተጨማሪ ከነ ኤልያስ ከድር መዝገብ አብዱል መጂድ አብዱል ከሪም፣ ሙባረክ፣ ቶፊቅ መሐመድ እና መሪማ ሐያቱ ከእስር መፈታታቸውንም ጨምረው ገልጠዋል። በእነ አቡበከር መሐመድ የክስ መዝገብ ከተካተቱት መካከል ያልተፈቱ አራት ሰዎች እንደሚቀሩ ጠበቃ አክለዋል።

ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW