1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

«የፖለቲካ ምህዳሩ ሙሉ በሙሉ ተዘግቷል» ግንቦት 7

ረቡዕ፣ መጋቢት 4 2011

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በተለይ ለDW በሰጡት ቃለ ምልልስ ዶክተር አብይ ስልጣን እንደያዙ የፖለቲካ ምህዳሩ መስፋት ቢጀምርም በየክልሉ ያሉ የኢህአዴግ አባላት ከቀደመው ሥርዓት በከፋ መልኩ ሙሉ ለሙሉ የፖለቲካ ምህዳሩን እንደዘጉት ይፋ አድርገዋል::የዜግነት ፖለቲካ አራማጅ ድርጅቶችን በጠላትነት ፈርጀው እንቅስቃሴያቸውን ገድበዋል ሲሉም ተናግረዋል።

Andargachew Tsige - Äthiopischer Politiker & Generalsekretär von Ginbot
ምስል Privat

«በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳሩ ሙሉ ለሙሉ ተዘግቷል» አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ

This browser does not support the audio element.

የኢትዮጵያ መንግሥት ካለው ጉልበት በላይ በፌደራሊዝም ሥርዓት ስም የራሳቸውን የደህንነት መዋቅር ወታደራዊ ኃይል እና በዘር ላይ የተመሰረተ ሚድያ ያደራጁ የክልል አስተዳደሮች በዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታው ላይ ትልቅ ማነቆ መፍጠራቸውን የአርበኞች ግንቦት 7 ከፍተኛ አመራር አስታወቁ:: የድርጅቱ ዋና ጸሃፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በተለይ ለ DW በሰጡት ቃለ ምልልስ ዶክተር አብይ ስልጣን እንደያዙ የፖለቲካ ምህዳሩ መስፋት ቢጀምርም በየክልሉ የሚገኙ የኢህአዴግ አባላት ከቀደመው ሥርዓት በከፋ መልኩ ሙሉ ለሙሉ የፖለቲካ ምህዳሩን እንደዘጉት ይፋ አድርገዋል:: እነዚህ አባላት የዜግነት ፖለቲካ አራማጅ ድርጅቶችን በጠላትነት ፈርጀው እንቅስቃሴያቸውን ገድበዋል ሲሉም ተናግረዋል። በዚህ የተነሳም የሕብረተሰቡም ሆነ የአገሪቱ ህልውና በአሁኑ ወቅት ከመቼውም ጊዜ በላይ ከፍተኛ አደጋ እና ስጋት ውስጥ ወድቋልም ብለዋል:: ዝርዝሩን እንዳልካቸው ፈቃደ አጠናቅሮታል::

እንዳልካቸው ፈቃደ

ኂሩት መለሰ

እሸቴ በቀለ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW