1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በኢትዮጵያ ድርቅና ተፅእኖዎቹ

እሑድ፣ ነሐሴ 17 2007

በድርቁ ምክንያት በቆላማ አካባቢዎች ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ የቀንድ ከብቶች ሞተዋል ። የዝናብ እጥረት ባስከተለው ድርቅ መንስኤ የምግብ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች ቁጥርም ቀደም ሲል ከተገመተው በላይ ሆኖ መገኘቱ ተነግሯል ።

Dürre – Äthiopien
ምስል European Commission DG ECHO / CC BY-SA 2.0

በኢትዮጵያ ድርቅና ተፅእኖዎቹ

This browser does not support the audio element.

በአንዳንድ የኢትዮጵያ ክልሎች ሊገባደድ ጥቂት ቀናት በቀሩት በ2007 ዓም የበልግ እንዲሁም የክረምቱ ዝናብ መዘግየቱና በበቂ መጠን አለመጣሉ የሰብል ምርት ላይ ተፅእኖ አሳድሯል ። የችግሩ ሰለባ የሆኑትም በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ፣ በሰሜን ምሥራቅ አማራ ክልል ፣ በደቡባዊ ትግራይ በአፋር እና በማዕከላዊና ምስራቅ ኦሮምያ ውስጥ የሚገኙ አካባቢዎች መሆናቸው ተገልጿል ። በድርቁ ምክንያት በቆላማ አካባቢዎች ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ የቀንድ ከብቶች ሞተዋል ። የዝናብ እጥረት ባስከተለው ድርቅ ምክንያት የምግብ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች ቁጥርም ቀደም ሲል ከተገመተው በላይ ሆኖ መገኘቱ ተነግሯል ።በመጢው እሁድ የሚተላለፈው እንወያይ በኢትዮጵያ ድርቅና ተፅእኖዎቹ ላይ ያተኩራል ። በውይይቱ ከተነሱት ሃሳቦች የሚከተሉት ይገኙበታል ።

ሒሩት መለሰ

እሸቴ በቀለ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW