በኢትዮጵያ ድርቅና ተፅእኖዎቹ
እሑድ፣ ነሐሴ 17 2007ማስታወቂያ
በአንዳንድ የኢትዮጵያ ክልሎች ሊገባደድ ጥቂት ቀናት በቀሩት በ2007 ዓም የበልግ እንዲሁም የክረምቱ ዝናብ መዘግየቱና በበቂ መጠን አለመጣሉ የሰብል ምርት ላይ ተፅእኖ አሳድሯል ። የችግሩ ሰለባ የሆኑትም በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ፣ በሰሜን ምሥራቅ አማራ ክልል ፣ በደቡባዊ ትግራይ በአፋር እና በማዕከላዊና ምስራቅ ኦሮምያ ውስጥ የሚገኙ አካባቢዎች መሆናቸው ተገልጿል ። በድርቁ ምክንያት በቆላማ አካባቢዎች ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ የቀንድ ከብቶች ሞተዋል ። የዝናብ እጥረት ባስከተለው ድርቅ ምክንያት የምግብ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች ቁጥርም ቀደም ሲል ከተገመተው በላይ ሆኖ መገኘቱ ተነግሯል ።በመጢው እሁድ የሚተላለፈው እንወያይ በኢትዮጵያ ድርቅና ተፅእኖዎቹ ላይ ያተኩራል ። በውይይቱ ከተነሱት ሃሳቦች የሚከተሉት ይገኙበታል ።
ሒሩት መለሰ
እሸቴ በቀለ