በኢንተርኔት ዋጋ ላይ የቀረበ ስሞታ
ሐሙስ፣ ሰኔ 13 2011ማስታወቂያ
“የኢንተርኔት ዋጋ አላግባብ እየተቆረጠብን ነው” የሚል ስሞታ በሰፊው እየተደመጠ ነው። “የ100 ብር ካርድ ተሞልቶ፣ ያውም ብቅ ጥልቅ ለሚል አገልግሎት፤ ቶሎ ያልቅብናል” በማለት ተገልጋዮች ያማርራሉ። “ለጥቂት አገልግሎት ከፍተኛ ገንዘብ እንድንከፍል እየተገደድን ነው” ሲሉ ከሚያማርሩ የኢትዮ ቴሌኮም የኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚዎች መካከል አንዱ በማህበራዊ መገናኛ ብዙሃን ትችቶችን በመጻፍ የሚታወቀው ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ አንዱ ነው።
የኔትወርክ መቆራረጡ ከሚያደርሰው ኢኮኖሚያው ጉዳት በላይ ሀሳብን በነጻ መግለጽ ላይ የተቃጣ ጥቃት ነው ይላል ጋዜጠኛው። የተማሪዎች ፈተና፣ ግጭት፣ የኃላፊዎች ጉብኝት እና ሌሎች ምክንያቶች እየተፈለገ ኢንተርኔት ከመዝጋት ሌላ የተሻለ አማራጭ መጠቀም ያስፈልጋል ይላል። የአዲስ አበባው ወኪላችን ዩሃንስ ገብረእግዚያብሔር ጋዜጠኛ ኤልያስን አነጋግሯል።
ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ።
ዩሃንስ ገብረእግዚያብሔር
እሸቴ በቀለ