1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሰሜን አሜሪካ ሊቃነ ጳጳሳት ጥሪ

ዓርብ፣ መስከረም 7 2014

ሊቃነ ጳጳሳቱ ለአሜሪካ መንግስት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊንከን እና ሌሎች ባለስልጣናት በፃፉት ደብዳቤ ዩናይትድስቴትስ የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ አስመልክቶ ይዘዋለች ያሉት አቋም ስጋት ያሳደረባቸው መሆኑን ገልፀዋል። የደሕንነት እና ፍትኅ ለትግራይ ምክትል ፕሬዝደንት "የአሜሪካ መንግሥት አቋም ግልጽ ነው።እንደግፈዋለን" ብለዋል

USA l Erzbischöfe der Äthiopisch-Orthodoxen Kirche
ምስል American Ethiopia Public Affairs Committee

የሰሜን አሜሪካ ሊቃነ ጳጳሳት ጥሪ

This browser does not support the audio element.

ዩናይትድስቴትስ በኢትዮጵያ ላይ የያዘችው አቋም አሳስቦናል ሲሉ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሰሜን አሜሪካ አስር ሊቃነ ጳጳሳት አመለከቱ። ሊቃነ ጳጳሳቱ ለአሜሪካ መንግስት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊንከን እና ሌሎች ባለስልጣናት በፃፉት ደብዳቤ ዩናይትድስቴትስ የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ አስመልክቶ ይዘዋለች ያሉት አቋም ስጋት ያሳደረባቸው መሆኑን ገልፀዋል።በአሜሪካና በካናዳ የሚገኙ የ11 አህጉረ ስብከት ሊቃነ ጳጳሳት ትናንት ከአሜሪካ ሕዝብ እንደራሴዎችና አማካሪዎቻቸው ጋር ዋሽንግተን ዲሲ ውስጥ በጉዳዩ ላይ  ተወያይተዋል።ሊቃነ ጳጳሳቱን ወክለው የኒውዮርክና አካባቢው ሃገረ ስብከት ሊቃነጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ለዶይቸ ቨለ በሰጡት መግለጫ በትናንቱ ውይይት በጎ ምላሽ መገኘቱን ተናግረዋል።

ደሕንነት እና ፍትኅ ለትግራይ

የደሕንነት እና ፍትኅ ለትግራይ ምክትል ፕሬዝደንት ፕሮፈሰር ሙሉጌታ ገብረእግዚዓብሔር በበኩላቸው "የአሜሪካ መንግሥት አቋም ግልጽ ነው። እኛም እንደግፈዋለን።" ሲሉ ተናግረዋል። ፕሮፈሰር ሙሉጌታ ለዶይቼ ቬለ "አንዱ የአሜሪካ መንግሥት እያለ ያለው ነጻ የሆነ ዓለም አቀፍ አካል ምርመራውን ያካሒደው ነው የሚለው። በዚህ ላይ ደግሞ የመንገዶች መዘጋት፣ የሰብዓዊ ዕርዳታ እንዳይገባ መከልከል፣ የመብራት መጥፋት፣ የስልክ መጥፋት፣ የቴሌኮምዩንኬሽን አውታሮች መዘጋጋት እንዲነሳ ነው ጥሪ እያቀረቡ ያሉት" ብለዋል።


ታሪኩ ኃይሉ 
ኂሩት መለሰ
እሸቴ በቀለ
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW