1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በአዲስ አበባ የኤርትራ ኤምባሲ ዳግም ተከፍቷል

ሰኞ፣ ሐምሌ 9 2010

ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ጦር ከተማዘዙ ወዲህ ተዘግቶ የነበረው የኤርትራ ኤምባሲ ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እና ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አወርቂ በተገኙበት እንደገና በይፋ ተከፍቷል። በመክፈቻው ሥነ-ስርዓት ላይ የኤርትራ ባንዲራ ዳግም በኤምባሲው የተውለበለበ ሲሆን የሀገሪቱ ብሔራዊ መዝሙርም ተዘምሯል።

Äthiopien Eritrea eröffnet Botschaft beim einstigen Kriegsgegner
ምስል Fitsum Arega/Prime Minister Office Ethiopia

የኤርትራ ኤምባሲ ዳግም መከፈት

This browser does not support the audio element.

ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ጦር ከተማዘዙ ወዲህ ተዘግቶ የነበረው የኤርትራ ኤምባሲ ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እና ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አወርቂ በተገኙበት እንደገና በይፋ ተከፍቷል። በመክፈቻው ሥነ-ስርዓት ላይ የኤርትራ ባንዲራ ዳግም በኤምባሲው የተውለበለበ ሲሆን የሀገሪቱ ብሔራዊ መዝሙርም ተዘምሯል። በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ አጠገብ የሚገኘው የኤርትራ ኤምባሲ ቅጽር ግቢ ለበርካታ ዓመታት ከአገልግሎት ውጭ ሆኖ ከቆየ በኋላ የኢትዮጵያ ወጣቶች ፌዴሬሽን እንዲገለገልበት ተፈቅዶለት ይጠቀምበት እንደነበር ይታወሳል።

በዚሁ በኤርትራ ኤምባሲ ዳግም መከፈት ላይ አራማጆች (አክቲቪስቶች) ሀሳባቸውን ለዶይቼ ቬለ አካፍለዋል። አስተያየቶቹን ለማድመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ። 

ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር

ተስፋለም ወልደየስ

አዜብ ታደሰ  

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW