በኦሮምያ የአንድ የግል እጩ የምርጫ ተሞክሮ
ሰኞ፣ ሐምሌ 5 2013![Äthiopien | Parlamentswahl | Wähler in Agaro](https://static.dw.com/image/57984466_800.webp)
ማስታወቂያ
ባለፈው ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም በተካሄደው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ብሔራዊ ምርጫ በኦሮሚያ ክልል በግላቸው ተወዳድረው የፓርላማ መቀመጫ ያሸነፉ 3 ፖለቲከኞች ማንነት ይፋ ሆኗል። ታዋቂ ተቀናቃኝ የፖለቲካ ድርጅቶች አልተፎካከሩም የሚል ስሞታ በሚቀርብበት በክልሉ የቀድሞው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ከፍተኛ አመራሮች ዶ/ር ዲማ ነገዎ እና አቶ ገላሳ ዲልቦ እንዲሁም ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ ሶስቱን የፓርላማ ወንበር አሸንፈዋል።የግል እጩዎቹ ስላለፉባቸው የፖለቲካ ሂደትና ስለቀጣዩ ትንቢያ ከአሸናፊዎቹ አንዱን የአዲስ አበባ ዘጋቢያችን ስዩም ጌቱ አነጋግሯቸዋል።
ስዩም ጌቱ
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ