1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

በወለጋ የመጓጓዣ ዋጋ መናር

ረቡዕ፣ ሐምሌ 16 2017

ከደምቢዶሎ ጊምቢ መደበኛ የመጓጓዣ ዋጋ 400 ብር ነው።ይሁንና ተጓዦች እንደሚሉት አሁን 650 ብር ሆኗል። ለዚህም የነዳጅ ዋጋ መጨመር፣ የአቅርቦት ችግር እና እጥረት በምክንያትነት ይጠቀሳል፡፡ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሺ ዞን ደግሞ የመንገድ ችግር እና ከክረምት ጋር ተያይዞ የወንዝ ሙላት በትራንስርት አገልግሎት ላይ ተጽእኖ እያሳደረ ነው።

Äthiopien Dese 2024 | Transportverbot durch Fano-Milizen in Stadt und Busbahnhof
ምስል፦ Esayas Gelaw/DW

በወለጋ የመጓጓዣ ዋጋ መናር

This browser does not support the audio element.

በወለጋከዶምቢዶሎ ከተማ ወደ ነቀምት እንዲሁም ወደ ጊምቢ ለመጓጓዝ ከመደበኛ ታሪፍ በላይ ዋጋ እንደሚከፍሉ ነዋሪዎች በምሬት ይናገራሉ። ከዚህ ቀደም ዶቼቬለ ባቀረበው ዘገባ ዋጋው ይስተካላል ተብሎ ነበር ፤ሆኖም አሁንም ዋው አልቀነሰም፡፡ ለአብነት ያህል ከደምቢዶሎ ጊምቢ መደበኛ የመጓጓዣ ዋጋ 400 ብር ነው ይሁንና ተጓዦች አሁን እንደሚሉት አሁን 650 ብር ነው የሚከፍሉት፡፡

ለዚህም የነዳጅ ዋጋ መጨመር፣ የአቅርቦት ችግር እና እጥረት በምክንያትነት ይጠቀሳል፡፡ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልልካማሺ ዞን  ደግሞ የመንገድ ችግር እና ከክረምት ጋር ተያይዞ የወንዝ ሙላት በትራንስርት አገልግሎት ላይ ተጽእኖ እያሳደረ ነው። በነዚህ አካባቢዎች ስላለው የመጓጓዣ ችግር የነዋሪዎች ሮሮ እና መፍትሄ ስለሚባለው የአሶሳውን ወኪላችንን ነጋሳ ደሳለኝን በስልክ አነጋግሬዋለሁ።

ነጋሳ ደሳለኝ

ኂሩት መለሰ

አዜብ ታደሰ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ
ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW