1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ስለደመወዝ ጭማሪው የሕዝብ አስተያየት

ሥዩም ጌቱ
ረቡዕ፣ ነሐሴ 14 2017

የደመወዝ ጭማሪ ለሠራተኛው መልካም ከመሆኑም በላይ አንገብጋቢ ነው የሚሉት አስተያየት ሰጪዎቹ ሆኖም ጭማሪው ብቻውን በቂ አለመሆኑን ገልጸዋል፡፡ የደመወዝ ጭማሪው ለዋጋ ንረት ምክንያት ሆኖ ማህበረሰቡ ላይ ተጨማሪ ጫና አንዳይከሰት በአቅርቦትና መሰል ስራዎች ላይ ተገቢ ቁጥጥር ላይ ይበልጥ መሰራት እንዳለበት የነዋሪው አብይ ጥያቄ ነው፡፡

Äthiopien | Geldscheine Währung
ምስል፦ MICHELE SPATARI/AFP

ስለደመወዝ ጭማሪው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች አስተያየት

This browser does not support the audio element.

በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ መንግስት ከመጪው መስከረም ጀምሮ በተለይ ለመንግስት ሰራተኞች የደመወዝ ጭማሪ እንደሚደርግ በይፋ አስታውቋል፡፡ይህ የደመወዝ ጭማሪ ለሠራተኛው መልካም ከመሆኑም በላይ አንገብጋቢ ነው የሚሉት አስተያየት ሰጪ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች፤ ነገር ግን የደመወዝ ጭማሪ ብቻውን በቂ አለመሆኑን በአስተያየታቸው ገልጸዋል፡፡

የደመወዝ ጭማሪው ለዋጋ ንረት  ምክንያት ሆኖ ማህበረሰቡ ላይ ተጨማሪ ጫና አንዳይከሰት በአቅርቦትና መሰል ስራዎች ላይ ተገቢ ቁጥጥር ላይ ይበልጥ መሰራት እንዳለበት የነዋሪው አብይ ጥያቄ ነው፡፡

ከደመወዝ ጭማሪው ይልቅ የግብር እና ተያያዥ ወጪውች ቅነሳ እና የሰራተኛው ጥቅማጥቅም ላይም መስራት አስፈላጊ መሆኑን ነዋሪዎቹ አስተያየት ሰጥተዋል። ሥዩም ጌቱ ከአዲስ አበባ ተከታዮቹን የህዝብ አስተያየቶች አሰባስቧል።

 

ሥዩም ጌቱ

ኂሩት መለሰ

ልደት አበበ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW