1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ወደ ሀገር ቤት ገብቷል

ሰኞ፣ መስከረም 1 2010

ከአዲስ አበባ ቀይ ባህርን ተሻግረን ወደ የመን እናቀናለን፡፡ የመን በጦርነት፣ በሽታ እና ረሃብ አበሳዋን እያየች ነው፡፡ በቀድሞ መንግስት ደጋፊዎች እና በአማጽያን መካከል አላባራ ያለው ጦርነት በሀገሪቱ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን መፈናፈኛ አሳጥቷቸዋል፡፡ በዚህ አይነት አጣብቂኝ ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውየን አዲስ አመትን እንዴት ተቀበሉት?

11.08.2013 DW online Karte Jemen, Saana, Balhaf eng

አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ወደ ሀገር ቤት ገብቷል

This browser does not support the audio element.

የመን በጦርነት ላይ ነች፡፡ የሳዑዲ አረቢያ መራሹ ጦር በየጊዜው የአየር ድብደባ ይፈጽመባታል፡፡ በሀገሪቱ የተዛመተው ወረርሽኝ ከግማሽ ሚሊዮን ህዝብ በላይ ለህመም መዳረጉ ተዘግቧል፡፡ እንዲህ አይነት ችግሮች በተደራረቡባት የመን ኢትዮጵያውያን የአዲስ ዓመት በዓልን እንዴት እያከበሩ ነው? ጥያቄው የቀረበለት የሰንአውን ወኪላችንን ግሩም ተክለ ሃይማኖት “ኢትዮጵያውያን ተሰባስበው በዓሉን ቢያከብሩም አከባበሩ ከበፊቱ በጣም ቀዝቅዟል” ይላል፡፡ አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ወደ ሀገር መግባቱን የሚናገረው ግሩም በኢኮኖሚ ችግርም፣ በስራ ማጣትም “ቀዝቀዝ ብሎ ወዙ መፍዘዙ አልቀረም” ሲል በየመን ያለውን ሁኔታ ያስረዳል፡፡   

 

ግሩም ተክለ ሃይማኖት 

ተስፋለም ወልደየስ

ኂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW