በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የተከሰተው ቀውስ መባባሱ
ሰኞ፣ ኅዳር 1 2001ማስታወቂያ
በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ምስራቃዊ ክፍል፤ በመንግስት እንደሚደገፉ በሚነገርላቸው ሃይላትና አማፅያን መካከል ያገረሸው ብጥብጥ አዲስ አሰላለፍ መያዙ ተነገረ። የደቡብ አፍሪቃ አገራት በቦታው ሠላም አስከባሪ ሃይላት፣ ጎረቤት አገር አንጎላ ደግሞ ወታደሮቿን ለመላክ እንደተዘጋጁ ገልፀዋል። የአማፅያኑ መሪ ላውሬንት ንኩንዳ በበኩላቸው፤ ጦር ልኬ እዋጋለሁ ብሎ የደፈረ ሁሉ እንደ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ መንግስት የሀፍረት ማቅ ይከናነባል ሲሉ ዝተዋል። ዝርዝሩን ማንተጋፍቶት ስለሺ እንደሚከተለው አቀናብሮታል። ◄