1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

በጃፓን ያልተሳካው የኢትዮጵያ አትሌቶች ተልዕኮ

ቅዳሜ፣ መስከረም 10 2018

ኢትዮጵያ ስትካፈልበት ከሰነበተችው 20ኛው የቶኪዮ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የወርቅ ሜዳሊያ ሳታገኝ የመጨረሻውን ቀን እየጠበቀች ነው። ዛሬ ኢትዮጵያዉያ ሜዳሊያ ልታገኝ ትችላለች ተብሎ ተስፋ የተጣለበት የሴቶች የ5000 ሜትር ውድድር ያለ ሜዳሊያ ተጠናቋል።

በጃፓን ያልተሳካው የኢትዮጵያ አትሌቶች ተልዕኮ
ኢትዮጵያዉያ ሜዳሊያ ልታገኝ ትችላለች ተብሎ ተስፋ የተጣለበት የሴቶች የ500 ሜትር ውድድር ያለ ሜዳሊያ ተጠናቋል።ምስል፦ Stefan Mayer/Eibner/IMAGO

ለኢትዮጵያ አትሌቶች ዉጤት ማጣት ምክንያቱ ምን ይሆን ?

This browser does not support the audio element.

ኢትዮጵያ ስትካፈልበት ከሰነበተችው 20ኛው የቶኪዮ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና  የወርቅ ሜዳሊያ ሳታገኝ የመጨረሻውን ቀን እየጠበቀች ነው። ዛሬ ኢትዮጵያዉያ ሜዳሊያ ልታገኝ ትችላለች ተብሎ ተስፋ የተጣለበት የሴቶች የ5000 ሜትር ውድድር ያለ ሜዳሊያ ተጠናቋል።

በውድድሩ ሜዳሊያ የማግኘት ቅድመ ግምት አግኝታ የነበረው ጉዳፍ ጸጋይ አምስተኛ በመሆን አጠናቃለች። ኬንያዉያኑ ብአትሪክ ቺቤት  እና ፌዝ ኪፒገን የወርቅ እና የብር ሜዳሊያውን ለኬንያ አስገኝተዋል።

በቶኪዮ የዓለም ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ለሜዳሊያ ብቸኛ ተስፋ የሰነቀችበት ነገ እሁድ የሚካሄደው የወንዶች የአምስት ሺ ሜትር ውድድር ብቻ ነው ፤ እሱም ቢሆን በጠባብ ዕድል። ለመሆኑ ኢትዮጵያ በሃያኛው የዓለም  የአትሌቲክስ  ሻምፒዮና ላይ ለምን ዉጤት አጣች ? የመስኩ ባለሞያዎችስ በዚህ ላይ ምን ይላሉ ?

ኃይማኖት ጥሩነህ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW