1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

በጋምቤላ ክልል የኮሌራ ስርጭት እየጨመረ ነው

ሐሙስ፣ የካቲት 20 2017

በጋምቤላ እስካሁን 23 ሰዎች በኮሌራ መሞታቸውን የተናገሩት አንድ የጤና ባለሙያ በሽታውን ለመከላከል አንድ የግል ተቋም ድጋፍ ማድረጉን እና በዓለም ጤና ድርጅት የህክምና ድጋፍ መሰጠቱን አብራርተዋል፡፡ ከደቡብ ሱዳን አጎራባች አኮቦ ወረዳ ለመጀመሪያ ጊዜ መከሰቱ በተነገረው nበሽታው ብዙ ሰዎች የተጠቁት ዋንቱዋ በተባለ ወረዳ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

Äthiopien Gambella 2025 | Cholera-Ausbruch | Gesundheitsamt bestätigt Epidemie
ምስል፦ Gambella Health Bureau

በጋምቤላ ክልል የኮሌራ ስርጭት እየጨመረ ነው

This browser does not support the audio element.

የበሽታው ስርጭት እየጨመረ ነው

በጋምቤላ ክልል ኑዌር ብሔረሰብ ዞን  ውስጥ በስፋት እየተስተዋለ ነው የተባለው የኮሌራ በሽታ የስርጭቱን አድማስ በማስፋት በጋምቤላ ከተማ እና ሶስት የስደተኞች ጣቢያዎች ውስጥ በሽታው መከሰቱን የክልሉ መንግስት አመልክተዋል፡፡ በክልሉ ጤና ቢሮ መረጃ መሰረት እስካሁን በክልሉ ደረጃ  ከ3 መቶ በላይ ሰዎች በበሽታው መያዛቸውን ይፋ ተደርገዋል፡፡ በጋምቤላ ክልል እስከ ትናንት ምሽት በዋንቱዋ ወረዳ በጤና ተቋማት ውስጥ በበሽታው የሰው ህይወት ማለፉን ያነጋርናቸው ጤና ባለሙያዎች ገልጸዋል፡፡ በኮሌራ በሽታ የተጠቁ ሰዎች ለማከም የሚያስችል የተለያዩ ጊዜያዊ ማከሚያ ቦታዎች ተዘጋጅቶ አገልግሎት እየተሰጠ እንደሚገኝ አመልክተዋል፡፡የኮሌራ በሽታ በጋምቤላ ኑዌር ዞን መከሰቱ ተረጋገጠ

በጋምቤላ ክልል እስካሁን 23 ሰዎች በበሽታው ህይወታቸው ማለፉን በዝርዝር የተናገሩት አንድ የጤና ባለሙያ በሽታውን ለመከላከል አንድ የግል ተቋም ድጋፍ ማድረጉን እና በዓለም ጤና ድርጅት ድጋፍ የተደረገላቸውን ስፍራዎች የህክምና ድጋፍ መሰጠቱን አብራርተዋል፡፡ ከደቡብ ሱዳን አጎራባች በሆነው አኮቦ በተባለ ወረዳ በኩል ለመጀመሪያ ጊዜ መከሰቱን የተነገረው በሽታው በብዛት ብዙ ሰዎች የተጠቁት ደግሞ ዋንቱዋ የተባለ ወረዳ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ አብዛኛው ሰዎች በበሽታው ክፉኛ ከተጎዱ በኀላ ወደ ህክምና ተቋማት እንደሚመጡ በመጥቀስ ከክልና ሌሎች ዞኖች የጤና ባለሙያዎችም ለህክምና እገዛ በተለያዩ ቦታዎች እንዲሰማሩ መደረጉንም ጠቁመዋል፡፡በጋምቤላ ኮሌራ መሰል በተባለ በሽታ የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት አለፈ

ከ3 መቶ በላይ ሰዎች በበሽታው ተይዘዋል

በጋምቤላ የተከሰተውን የኮሌራ በሽታ አስመክልቶ መረጃን እንዲሰጡን ከክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ መረጃ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም፡፡ በክልሉ ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር ኃላፊ ኝኪዎ ጊሎ ከዚህ ቀደም በሰጡን መረጃ በክልሉ በሽታውን ስርጭት ለመከላል ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ በመግለጽ በበሽታው የደረሰውን ጉዳት ግን ለጊዜው መግለጽ አልፈለጉም፡፡

የክልሉ መንግስት ከአምስት ቀን በፊት የካቲት 15/2017 ዓ.ም በሽታው ከተከሰተ ጊዜ አንስቶ 334 ሰዎች በበሽታው መጠቃቻውንና 15 ሰዎች ደግሞ ህይወት ማለፉን አመልክተዋል፡፡ ስርጭቱም ስደተኞች ካምፕን ጨምሮ  ወደ ተለያዩ ቦታዎች መስፋፋቱን የክልሉ መንግስት መረጃ ያመልክታል፡፡ ከዓለም ጤና ድርጅት ድጋፍ በተጨማሪም በሽታውን ለመከላል የክልሉ መንግስት 5 ሚሊዩን ብር መድቦ እየሰራ እንደሚገኝ ተገልጸዋል፡፡

ነጋሳ ደሳለኝ

ኂሩት መለሰ

ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW