1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በግብፅ ባለስልጣናቱ እገዳ ተጣለባቸው

ቅዳሜ፣ የካቲት 5 2003

የግብፅ ጦር በቀድሞ ፕሬዚዳንት ሆስኒ ሞባረክ 20 ታማኞች ላይ የጉዞ እገዳ አስቀመጠ። የጎዞ እገዳውን ያስተላለፈው የግብፅ ጦር ሲሆን፤ ባለስልጣናቱ ሀገር ለቀው እንዳይሸሹ በሚል ያስተላለፈው ውሳኔ እንደሆነም ተጠቅሷል።

ግብፃውያን በደስታ ተውጠው
ግብፃውያን በደስታ ተውጠውምስል dapd
ባለስልጣናቱ መጓዝ ከፈለጉም ከጦሩ ፍቃድ ማግኘት እንዳለባቸው ተጠቁሟል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የቀድሞው የግብፅ ፕሬዚዳንት ሆስኒ ሞባረክ የት እንዳሉ በውል ለማወቅ አልተቻለም። አንዳንዶች ሻርም አል ሼክ ወደተሰኘችው ሌላኛዋ የግብፅ ከተማ ተዛውረዋል ሲሉ ይደመጣሉ። የአረብ ብዙኋን መገናኛ ደግሞ ሙባረክ ከሀገር ወጥተው ወደ አውሮፓ፣ አለያም ከባህረ-ሰላጤው ሀገራት ወደ አንዱ ሳያቀኑ አልቀሩም ይላሉ። ማንተጋፍቶት ስለሺ
ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW