በግብፅ የምክር ቤት ምርጫና ውዝግቡ
ማክሰኞ፣ ኅዳር 21 2003ማስታወቂያ
ከትናንት በስተያ በግብፅ በተካሄደው የምክር ቤት ምርጫ ተቃዋሚዎች እንግልት እንደተፈጸመባቸው ገለፁ። በአንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች ድብደባ ጭምር እንደነበረም ተዘግቧል። በተለይ በወደብ ከተማይቱ አሌክዛንደሪያ የተቃዋሚ ፓርቲ የምርጫ ታዛቢዎች በምርጫ ጣቢያ እንዳይገቡ መታገዳቸውም ተጠቅሷል። በግብፅ ዋነኛው የተቃዋሚ ፓርቲ እንደሆነ የሚነገርለት ሙስሊም ወንድማማችነት ፓርቲ ምርጫው የተጭበረበረና ተቀባይነት የሌለው ነው ሲል ትናንት አስታውቋል።
ማንተጋፍቶት ስለሺ
አርያም ተክሌ