በፈረንሳይ የተገን ጠያቂዎች ይዞታ
ሐሙስ፣ ሚያዝያ 23 2006ማስታወቂያ
በጎርጎሮሳውያኑ 2013 በአውሮፓ ተገን እንዲሰጣቸው ማመልከቻ ያስገቡ ስደተኞች ቁጥር ከ2012 በ10 በመቶ ብልጫ እንዳለው ዩሮስታት የተባለው የአውሮፓ የስታትስቲክስ ፅህፈት ቤት አስታውቋል ። በ2013 በርካታ የተገን ጠያቂዎች ማመልከቻዎች ከቀረቡላቸው ሃገራት መካከል ጀርመን ግብራ ቀደሙን ቦታ ስትይዝ ፈረንሳይ ስዊድንና ብሪታኒ በቅደም ተከተል ጀርመንን ይከተላሉ ። ከነዚህ መካከል በተለይ ፈረንሳይ ከቀረቡላት ማመልከቻዎች የተቀበለችው ቁጥር ዝቅተኛ መሆኑ አስተችቷታል ። ከዚህ ሌላ ፈረንሳይ ተገን ጠያቂዎችን የምትይዝበት መንገድም ኢትዮጵያውያን ተገን ጠያቂዎችን አማሯል ።የፓሪሷ ወኪላችን ሃይማኖት ጥሩነህ ዝርዝር አገባ አላት ።
ሃይማኖት ጥሩነህ
ሂሩት መለሰ
ተክሌ የኋላ