በ2017 የታሰሩ ጋዜጠኞች ብዛት
ረቡዕ፣ ታኅሣሥ 4 2010ማስታወቂያ
ባገባደድነዉ የጎርጎሪያን 2017 ዓመት የታሰሩት ጋዜጠኞች ቁጥር አምና ታስረዉ ከነበሩት መጨመሩን CPJ በሚል ምሕፃረ ቃል የሚጠራዉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ኮሚቴ አስታወቀ። ኮሚቴዉ ዛሬ ይፋ ባደረገዉ ዓመታዊ ዘገባዉ እንዳስታወቀዉ ዘንድሮ በመላዉ ዓለም የታሰሩት ጋዜጠኞች 262 ናቸዉ። አምና በርካታ ጋዜጠኞችን በማሰር ከአፍሪቃ የሰወስተኝነቱን ደረጃ ይዛ የነበረችዉ ኢትዮጵያ ዘንድሮ ደረጃዋን ለሌላ ለቅቃለች። ግብፅ እና ኤርትራ ግን በርካታ ጋዜጠኞችን በማሰር ዘንድሮም እንዳምናዉ የመጀመሪያ እና ሁለተኛዉን ሥፍራ እንደያዙ ናቸዉ። የዋሽግተን ዲሲ ዘጋቢያችን መክብብ ሸዋ ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።
መክብብ ሸዋ
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ