ቡና በዓለም ገበያ
ረቡዕ፣ የካቲት 10 2013![Kafeeernte in Äthiopien](https://static.dw.com/image/47090797_800.webp)
ማስታወቂያ
የተጠቃሚው ቁጥር እዚህ ጨምሮ የቡና ዋጋ በየጊዜው ወደላይ እየመጠቀ ነው። ግንቡ ፈርሶ የምሥራቅ አውሮጳና የእስያ ነዋሪዎች ቡና ጠጪ ከሆኑ ወዲህ ደግሞ ገበያው ደርቷል። በተቃራኒው አምራቹ ገበሬ ከቡና ለቃሚው ጋር ከቡና ሽያጭ የሚያገኘው ገንዘብ ወደታች በየጊዜው እያሽቆለቆለ ይገኛል። የቡና አምራች ሃገራት ገበሬዎች ያመረቱትን ቡና ቆልተውና ፈጭተው በማሸግ ለገበያ ከሚያቀርቡት ኩባንያዎች እጅግ ያነሰ ገቢ እንደሚያገኙ በየጊዜው ይነገራል። በተለይም በአውሮጳና በሰሜን አሜሪካ የቡና ገበያውን ለተመለከተ በሚሊየኖች የሚቆጠር ዶላር እንደሚዛቅበት ያስተውላል።
ይልማ ኃይለ ሚካኤል
ሸዋዬ ለገሠ