ባርነት በሀያ አንደኛው ክፍለ ዘመን
ሰኞ፣ ሐምሌ 13 2001ማስታወቂያ
በተለይ በቤት ሰራተኝነት በሆቴል ቤቶች በምግብ አብሳይነት እንዲሁም በግንባታ ስራ ላይ የተሰማሩ አንዳንድ የውጭ ዜጎች መብታቸውን ባለማወቅ እንደሚበዘበዙ ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች በሚያወጧቸው አንዳንድ ዘገባዎች ላይ ተመልክቷል ። ይህን መሰሉን ድርጊት የሚከታተለው የጀርመን የስብዓዊ መብት ተቆርቋሪ ድርጅት የጉልበት ብዝበዛውን ለመከላከል ልዩ ልዩ ጥረቶችን ከማድረጉም በላይ የችግሩን ሰለባዎችም እየረዳ ነው ። እዚህ ጀርመን ውስጥ በትውልደ ኢትዮጵያዊ በዜግነት ጀርመናዊ በሆኑ ግለሰብ የኢትዮጵያ ምግብ ቤት ውስጥ በምግብ አብሳይነት ሲያገለግሉ የቆዩት አንዲት ኢትዮጵያዊት ከአሰሪያቸውዋ ይሰጣቸው በነበረው አነስተኛ ክፍያ እና ደረሰብኝ ባሉት የስራ በደል መንስኤ በዚህ ድርጅት ዕርዳታ ከሰው ተፈርዶላቸዋል ። ልደት አበበ በጀርመን በዚህ መልኩ የሚፈፀም ብዝበዛን ለመከላከል የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶችን ተግባርና የኢትዮጵያዊቷን ጉዳይ የተመለከተ ዘገባ አጠናቅራለች ።
ልደት አበበ ፣ ሂሩት መለሰ