ብሔርን መሠረት ያደረጉ መገናኛ ብዙሃንን የተመለከተው ውይይት
ዓርብ፣ ነሐሴ 28 2013ማስታወቂያ
በኢትዮጵያ ብሔርን መሠረት ያደረጉ የመገኛኛ ብዙሃን አውታሮች በአይነትና በመጠን እየተበራከቱ መምጣታቸው ዘርፉ በተስፋም ፣ በስጋትም የተሞላ እንዲሆን እያደረገው መሆኑ ተገለጸ። «ብሔርና የኢትዮጵያ መገኛኛ ብዙሃን» በሚል ርዕስ ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በሀዋሳ ከተማ ከሰሞኑ ተካሂዷል። በውይይት መድረኩ ላይ ብሔርን መሠረት ባደረጉ የመገኛኛ ብዙሃን አውታሮች ላይ የተካሄደ ጥናት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። የመድረኩ አዘጋጆች በቀጣይም በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ተመሳሳይ ውይይት ለማካሄድ ዕቅድ መኖሩን መጠቆማቸውን ከሀዋሳ ሸዋንግዛዉ ወጋየሁ በላከልን ዘገባ አመልክቷል።
ሸዋንግዛዉ ወጋየሁ
ሸዋዬ ለገሠ
ኂሩት መለሰ