1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ተላላፊ በሽታዎች በኢትዮጵያ

ሐሙስ፣ መጋቢት 22 2008

የየአካባቢዉ ነዋሪዎችና አንዳድ የዜና ምንጮች «ኮሌራ» የሚሉት በሽታ አንዳድ አካባቢዎች በርካታ ሰዉ ገድሏል። የኢትዮጵያ መንግሥት ግን ለበሽታዉ አጣዳፊ ተቅማጥና ትዉከት የሚለዉን ሥም ነዉ የመረጠዉ

ምስል picture-alliance/Dr.Gary Gaugler/OKAPIA

[No title]

This browser does not support the audio element.

ኢትዮጵያ ዉስጥ በደቡብ፤ በኦሮሚያ እና በሶማሌ መስተዳድር የተዛመተዉ የተቅማጥና ትዉከት በሽታ የሰዉ ሕይወት ማጥፋቱ ተዘገበ። የየአካባቢዉ ነዋሪዎችና አንዳድ የዜና ምንጮች «ኮሌራ» የሚሉት በሽታ አንዳድ አካባቢዎች በርካታ ሰዉ ገድሏል። የኢትዮጵያ መንግሥት ግን ለበሽታዉ አጣዳፊ ተቅማጥና ትዉከት (አተት) የሚለዉን ሥም ነዉ የመረጠዉ። የጤና ጥበቃ ሚንስቴር እንዳስታወቀዉ በድርቁ እና በንፅሕና ጉድለት ምክንያት ከተቅማጥና ትዉከቱ በተጨማሪ የማጅራት ግትር (ሜኔን ጃይትስ) በሽታም በተለያዩ አካባቢዎች ተከስቷል። በበሽታዉ ሥለሞቱ ወይም ሥለታመሙ ሰዎች ብዛት ግን በግልፅ የተነገረ ነገር የለም። የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ጌታቸዉ ተድላ ሐይለ ጊዮርጊስ ዝርዝሩን ልኮልናል።

ጌታቸዉ ተድላ ሐይለ ጊዮርጊስ

ነጋሽ መሐመድ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW