1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ተቃውሞ ለንደን በሚገኘው የሊቢያ ኤምባሲ

ቅዳሜ፣ ኅዳር 30 2010

በሊቢያ ያለውን የአፍሪቃውያን ባርነት በመቃወም ዛቴ የብሪታንያ መዲና ለንደን ከተማ በሚገኘው የሊቢያ ኤምባሲ ደጃፍ የተቃውሞ ሰልፍ ተካሂዷል። የተቃውሞ ሰልፉ የተጠራው «ብሔራዊ ጸረ-ባርነት» በተባለው ግብረ-ኃይል ነው። በተቃውሞ ሰልፉ አያሌ ኢትዮጵያውያንም ተሳታፊ ነበሩ።

Marokko Proteste gegen Sklaverei in Libyen
ምስል Getty Images/AFP/F. Senna

በሊቢያ ያለውን ባርነት በመቃወም የለንደን ሰልፍ

This browser does not support the audio element.

በሊቢያ የሚገኘውን የአፍሪቃውያን ባርነት በመቃወም ዛሬ የብሪታንያ መዲና ለንደን ከተማ በሚገኘው የሊቢያ ኤምባሲ ደጃፍ የተቃውሞ ሰልፍ ተካሂዷል። የተቃውሞ ሰልፉ የተጠራው «ብሔራዊ ጸረ-ባርነት» በተባለው ግብረ-ኃይል ነው። ተቃውሞው በተለይ በአፍሪቃ ምድር ባርነት ሲከወን የአፍሪቃ ኅብረት ቸልተንነት በመንቀፍ ያተኮረ ነበር። በብሪታንያ እና በፈረንሳይ መንግሥት ላይ ሰልፈኞች ቁጣቸውን ገልጠዋል። ምስቅልቅሏ በወጣው ሊቢያ ውስጥ አፍሪቃውያን በሊቢያ ዜጎች ለባርነት እየተሸጡ ነው የሚለው ዜና በቪዲዮ ታጅቦ በሲኤን ኤን ማሰራጪያ በኩል ይፋ ከወጣ በኋላ የተቀሰቀሰው ቁጣ ከየአቅጣጫው አልበረደም። በተቃውሞው ላይ በርካታ ኢትዮጵያውያንም ተሳታፊ ነበሩ። ድልነሳው ጌታነህ ሰልፉ በተካሄደበት ሥፍራ ተገኝቶ ያጠናቀረውን ዘገባ ከለንደን ልኮልናል።

ድልነሳው ጌታነህ

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW