ተገን ጠያቂዎችና የቀኝ አክራሪዎች ተቃውሞ
ዓርብ፣ ነሐሴ 17 2005ማስታወቂያ
በጀርመን መዲና በበርሊን፤ ሔለርስዶርፍ በተባለው የከተማይቱ ከፊል ይሠፍሩ ዘንድ ቤት የተዘጋጀላቸውን ተገን ጠያቂ የውጭ ተወላጆች፣ በመቃወም የቀኝ አክራሪዎች ችግር ፈጥረዋል። ጠጋ ብለው ሳያውቁ፤ የቀኝ ጽንፈኛ አመለካከታቸውን ብቻ በማንጸባረቅ፤ የውጭ ተወላጆችን፣ በጭፍን የሚጠሉ ፣ የሚያጥላሉ አካራሪ ጀርመናውያን በየጊዜው ነው ተቃውሞአቸውን የሚያሰሙት። መቃወም ብቻም ሳይሆን፣ በየጊዜው የኃይል እርምጃ መውሰዳቸው አይዘነጋም። ስለ ሔለርስዶርፉ የቀኝ አክራሪዎች ተቃውሞ ፣ ተክሌ የኋላ ፤ የበርሊኑን ወኪላችንን ይልማ ኃይለ ሚካኤልን በስልክ አነጋግሮታል።
ተክሌ የኋላ ፤
ይልማ ኃይለ ሚካኤል