1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ተፈናቃይ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች 

ረቡዕ፣ ጥር 18 2014

ከ1500 የሚበልጡት ተማሪዎች እንደሚሉት አማራ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች መመደባቸዉን ትምሕርት ሚንስቴር ገልጦላቸዉ ነበር።ዩኒቨርስቲዎቹ ግን ተማሪ የመቀበል አቅም እንደሌላቸዉ ገልፀዉላቸዋል።

Äthiopien | Ehemalige Studenten der Tigray-Universität
ምስል Solomon Muchie/DW

የቀድሞ የትግራይ ዩኒቨርስቲዎች ተማሪዎች አቤቱታና መልሱ

This browser does not support the audio element.

ትግራይ ዉስጥ በሚደረገዉ ጦርነት ምክንያት በክልሉ ከሚገኙ የተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ሸሽተዉ ወደ መሐል ኢትዮጵያ የተመለሱ ተማሪዎች በሌሎች ዩኒቨርስቲዎች እንደሚመደቡ የተገባላቸዉ ቃል እስካሁን ድረስ ገቢር አለመሆኑን አስታወቁ።ከ1500 የሚበልጡት ተማሪዎች እንደሚሉት አማራ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች መመደባቸዉን ትምሕርት ሚንስቴር ገልጦላቸዉ ነበር።ዩኒቨርስቲዎቹ ግን ተማሪ የመቀበል አቅም እንደሌላቸዉ ገልፀዉላቸዋል።የባሕርዳርና የጎንደር ዩኒቨርስቲዎች ባለስልጣናት ዛሬ በተለይ ለዶቸ ቬለ እንደገለፁት ግን የተመደቡላቸዉን ተማሪዎች በቅርቡ እንደሚቀበሉ ቃል ገብተዋል።የትምህርት ሚንስቴር ባለስልጣናትም የተማሪዎቹ ችግር በቅርቡ እንደሚቃለል ተስፋ ሰጥተዋል።

ሰለሞን ሙጬ 

ነጋሽ መሐመድ

እሸቴ በቀለ
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW