ቱርክ ከ«አይሲስ» ጋር የሚታደርገዉ ትግል
ማክሰኞ፣ ኅዳር 14 2008ማስታወቂያ
በኢራቅና ሶርያ «እስላማዊ መንግስት» መስርቻለሁ የሚለው ጽንፈኛ ቡድን ታጣቂዎችንም ይሁን የጦር መሳሪያ ዝውውሩን ቱርክ እንድትቆጣጠር ለማድረግ ብዙ ውትወታን ፈልጋ ነበር። በስተመጨረሻ ቱርክ በጽንፈኛ ቡድኑ ላይ ወታደራዊ እርምጃ መውሰድ ጀምራለች። በሌላ በኩል በቱርክ የተለያዩ ከተሞች ሰሞኑን በ «አይሲስ» አሸባሪዎችና ደጋፊችን በማደን በተካሄደዉ አሰሳ ከሶስት ሽህ የሚበልጡ ታጣቂዎች ወደ ቱርክ ሀገር ዘልቀዉ እንዳይገቡ ባለፈዉ ዓመት የቱርክ መንግሥት እንዳደረገ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል። በዚህ በያዝነዉ የጎርጎርዮስ ዓመት ብቻ ከ 1000 የሚበልጡ ራሳቸዉን « እስላማዊ መንግሥት ነን ብለዉ የሚጠሩ አባላት ከነትጥቅ መሳርያና ቦንባቸዉ ድንበር ሊሻገሩ ሲሉ እንደተያዙ ተመልክቶአል።
ዩልያ ሃን / ይልማ ኃይለሚካኤል
እሸቴ በቀለ
አርያም ተክሌ