ታንዛንያና ባህሏ
ሐሙስ፣ ነሐሴ 16 2005ስምንት ጎረቤት ሀገራት እና የህንድ ውቅያኖስ የሚያዋስኗት ምስራቅ አፍሪቃዊት ሀገር ታንዛንያ ከቅኝ ገዢዋ ብሪታንያ ነፃ የወጣችው እኢአ ታህሳስ 9, 1961 ዓ ም ነበር። በታንዛኒያ ከስድስት ዓመት በፊት በተደረገ የህዝብ ቆጠራ ህዝቧ ከ41 ሚሊዮን በላይ እንደሆነ ተረጋግጧል። በሰሜን ታንዛንያ እና በጠረፍ አካባቢ በርካታ ሙስሊሞች ይኖራሉ። ከህብረተሰቡ ከ30-40 ከመቶው የእስልምና ዕምነት ተከታይ ነው። በዛንዚባር ደሰት እስከ 98 ከመቶው ሙስሊም ነው። በትልቁ የታንዛኒያ ግዛት ደግሞ የክርስትና ዕምነት ተከታዮች ይመረክታሉ። ከ 30-40 ከመቶው ካቶሊኮች ናቸው። በታንዛንያ በአጠቃላይ 128 የተለየያዩ ቋንቋዎችም ይነገራሉ።
ከመቶ ዓመታት በላይም ከአረብ ሀገሮች እና ቀድሞ እንደ ታንዛንያ በብሪታንያ ቅኝ ግዛት ስር ከነበረችው ህንድ ወደ ታንዛንያ የተሰደዱ ሰዎች በሀገሪቱ ይኖራሉ። ብዙ የህንድ ዝርያዎች በሀገሪቱ ስለሚኖሩም የምግብ እና የአሰራር ባህላቸው የሀገሬው አመጋገብ ላይ ይስተዋላል ወይም አስተዋፅዎ አድርጓል ይባላል።
ብዙ ቋንቋ እና ብሔር ስላላት ሀገር ባህል ወ/ሮ ጥሩ ወርቅ ወርቁ ያጫውቱናል። ወ/ሮ ጥሩ ወርቅ በዳሬ ሰላም ሲኖሩ 13 ዓመታት ተቆጥረዋል። እሳቸውም ታንዛኒያዊ ባለቤት እና ሁለት ልጆች አሏቸው።
ስለ ታንዛኒያ አመጋገብ፣ አለባበስ፣ የደስታ እና የሀዘን ጊዜ የመሳሰሉትን ነጥቦች ወ/ሮ ጥሩ አንስተንላቸዋል። ከድምፅ ዘገባው ያገኙታል።
ልደት አበበ
ተክሌ የኋላ