ታፍነዉ የተወሰዱት የጋምቤላ ሕጻናት
ሐሙስ፣ ሚያዝያ 27 2008ማስታወቂያ
ከደቡብ ሱዳን በመጡ የሙርሌ የጎሳ አባላት ታፍነዉ የተወሰዱት ሕጻናት አሉበት የተባለዉ ቦታ ከሰሜናዊ ከደቡብ ሱዳን መዲና ጁባ 300 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ መሆኑኑን የደቡብ ሱዳን መንግሥት ቃል አቀባይ አቴኔ ዌክ አቴኔ መግለፃቸዉ ሱዳን ትሪቡነ ዘግቦአል። እንደ ዘገባዉ የኢትዮጵያ መንግሥት ጦር ሠራዊት እቦታዉ ላይ በመገኘት ሁኔታዉን እየተቆጣጠረ መሆኑን የመንግሥት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸዉ ረዳ ማረጋገጣቸዉም ተዘግቦአል። በፌዴራል እና አርብቶ አደር ልማት ጉዳዮች ሚኒስትር የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ አበበ ወርቁ እንዳሉት ከጋንቤላ ታፍነዉ የተወሰዱት ሕጻናት ያሉበት ቦታ ታዉቋል።
አዜብ ታደሰ
ነጋሽ መሐመድ