1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ
ትምህርትኢትዮጵያ

«ወደ ዩንቨርሲቲ የሚገቡ ተማሪዎች ቁጥር አልቀነሰም» ሚኒስትር ደኤታ አቶ ኮራ ጡሸኔ

ልደት አበበ/ Lidet Abebe
ዓርብ፣ ሰኔ 6 2017

የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ደኤታ አቶ ኮራ ጡሸኔ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና ጋር በተያያዘ ስለተዘጉ የግል የትምህርት ተቋሟት ጉዳይ፣ የሀገሪቷ ትምህርት ጥራት እና የመምህራን ጉዳይን በሚመለከት ከዶይቸ ቬለ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል።

Äthiopien Addis Abeba 2024 | Chinesisch-Wettbewerb für äthiopische Studenten
ምስል፦ Michael Tewelde/Xinhua News Agency/picture alliance

«ወደ ዩንቨርሲቲ የሚገቡ ተማሪዎች ቁጥር አልቀነሰም» ሚኒስትር ደኤታ አቶ ኮራ ጡሸኔ

This browser does not support the audio element.

ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያ ውስጥ በቅርቡ 90 ያህል የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተዘግተዋል። የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ደኤታ አቶ ኮራ ጡሸኔ ከዶይቸ ቬለ ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ እንደተናገሩት ትምህርት ቤቶቹ የተዘጉት የትምህርት ሚኒስቴርን አሰራር መከተል ያልቻሉ ናቸው። « ትምህርት ሚኒስቴር ያደረገው የምታስተምሩትን ተማሪዎች ኦንላይን አስመዝግቡ ነው። ብዙዎቹ ግን ያ ፈተና ከመጣ ወዲህ ውጤታማነታቸው በጣም ስለቀነሰ፤ አንድም የማያሳልፉ እጅግ ብዙ ስለሆኑ በራሳቸው የተውት አሉ፤ ያ ማለት እንደ መዘጋት ነው።ግን ትምህርት ሚኒስቴር ከዚህ ጊዜ በኋላ ተዘግታችኋል ያላቸው አንድም የሉም። አሰራሩን መከተል ያልቻሉ በራሳቸው የወጡ ናቸው» ይላሉ።  
የመውጫ ፈተና መሰጠት ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ « ትምህርት ተለፍቶ የሚገኝ እንጂ በማጭበርበር አይገኝም» የሚል ባህሪ በተማሪዎች ዘንድ መታየት ጀምሯል የሚሉት ሚኒስትር ደኤታ አቶ ኮራ ተማሪዎችን ውጤታማ ለማድረግ እታች ያሉ ተማሪዎች ላይም እየተሰራ እንደሆ ገልፀዋል። ለዚህም በክፍል ውስጥ ያሉ ተማሪዎችን ቁጥር መቀነስ አንዱ መፍትሔ እንደሆነ ገልፀው ባለፉት ጥቂት ዓመታት ብቻ  በሺዎች የሚቆጠሩ ቅድመ 1ኛ  ወይም ኪንደር ጋርደኖች ተሰርተዋል ብለዋል።
« በየዩንቨርሲቲው  የማጠናከሪያ ትምህርት የሚከታተሉ ትልቅ ቁጥር ያላቸው ተማሪዎች አሉ» ። በማለት ሚኒስትር ደኤታ አቶ ኮራ ወደ ዩንቨርሲቲ የሚገቡ ተማሪዎች ቁጥርም አልቀነሰም ይላሉ።

የመምህራን ጉዳይ

በሀገሪቱ ያለውን የትምህርት ጥራት ለማሻሻል የሚደረገው ጥረት ከመምህራን አቅም ጋርም የተያያዘ ነው።  «መምህራን ላይ የኑሮ ጫና እንደሚኖር እንረዳለን » ሲሉ ለዶይቸ ቬለ የተናገሩት የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ደኤታ አቶ ኮራ  የመምህራን አመታዊ እርካታን በተመለከተ ጥናት እየተካሄደ እንደሆነ ይናገራሉ።  

ምስል፦ Alemnew Mekonnen/DW

በአማራ ክልል የሚገኙ የተማሪዎች እጣ ፈንታ

በአማራ ክልል በመቶዎች የሚቆጠሩ ትምህርት ቤቶች የሚገኙ ተማሪዎች ብሔራዊ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና አልወሰዱም። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተማሪዎች እስካሁን ከትምህርት ገበታቸው እንደተነጠሉ ይገኛሉ። አቶ ኮራ እንደ አንድ የትምህርት ሚኒስቴር አመራር አካል « ትምህርት ፖለቲካ መሆን እንደማይችል ሁሉም መረዳት አለበት« በማለት ችግሩ በትምህርት ሚኒስቴር  ብቻ ሊፈታ እንደማይችል በቃለ መጠይቁ ጠቁመዋል።

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW