1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ
ፖለቲካሰሜን አሜሪካ

ትራምፕ በዋሽንግተን ዲሲ ተግባራዊ ያደረጉት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ

ሐሙስ፣ ነሐሴ 8 2017

ትራምፕ የአሜሪካን ዋና ከተማ የዋሽንግተን ዲሲ ፖሊስ በፌደራሉ ፖሊስ ስር እንዲሆን መወሰናቸው እና ብሔራዊው ዘብ ከተማይቱ እንዲገባ ማድረጋቸው አሁንም ማወዛገቡ ቀጥሏል። ብሔራዊው ዘብ በዚህ ሳምንት ዋና ከተማይቱ መግባት ጀምሯል። ትራምፕ በከተማይቱ የሚገኙ ጎዳና ተዳዳሪዎችንም አነሳለሁ ማለታቸው ሕገ-መንግስታዊ ክርክሮችን አጭሯል።

ብሔራዊው ዘብ ከዚህ ሳምንት ማክሰኞ አንስቶ ወደ ዋና ከተማይቱ መግባት ጀምሯል።
ብሔራዊው ዘብ ከዚህ ሳምንት ማክሰኞ አንስቶ ወደ ዋና ከተማይቱ መግባት ጀምሯል። ምስል፦ Annabelle Gordon/REUTERS

ትራምፕ በዋሽንግተን ዲሲ ተግባራዊ ያደረጉት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ

This browser does not support the audio element.

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ወንጀል ተስፋፍቷል ባሉበት በዋሽንግተን ዲሲ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተግባራዊ ማድረጋቸው ቁጣና ተቃውሞ አስከትሏል። ትራምፕ የአሜሪካን ዋና ከተማ የዋሽንግተን ዲሲ ፖሊስ በፌደራሉ ፖሊስ ስር እንዲሆን መወሰናቸው እና ብሔራዊው ዘብ ከተማይቱ እንዲገባ ማድረጋቸው አሁንም ማወዛገቡ ቀጥሏል።

ብሔራዊው ዘብ ከዚህ ሳምንት ማክሰኞ አንስቶ ወደ ዋና ከተማይቱ መግባት ጀምሯል።  ከዚህ ሌላ ትራምፕ በከተማይቱ የተለያዩ ስፍራዎች የሚኖሩ ጎዳና ተዳዳሪዎችንም አነሳለሁ ማለታቸው ሕገ- መንግስታዊ ክርክሮችን አጭሯል። በትራምፕ ውሳኔና ውሳኔው ባስነሳቸው ውዝግቦች ላይ የዋሽንግተን ዲሲውን ዘጋቢያችንን አበበ ፈለቀን ስቲድዮ ከመግባቴ በፊት በስልክ አነጋግሬዋለሁ። 

አበበ ፈለቀ 

ኂሩት መለሰ

ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW