1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ኔዘርላንድስ የኤርትራን ዲፕሎማት ማባረሯ

ዓርብ፣ ጥር 11 2010

የኔዘርላድስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሀገሩ የሚገኙትን አንድ የኤርትራ ከፍተኛ ዲፕሎማት እንዲባረሩ መወሰኑን ትናንት በዓለም ዜና መዘገባችን ይታወሳል። ውሳኔው በውጭ ከሚገኙ የሀገሩ ተወላጆች የኤርትራ መንግሥት ዉጭ ሀገር የሚኖሩ ወይም ዲያስፖራ ማኅበረሰብ ላይ ከሚሰበስበው ግብር ጋር የተያያዘ መሆኑም ተገልጿል።

Eine afrikanische Insel der Architektur
ምስል፦ DW/Y.Tegenewerk

«ምክንያቱ ውጭ ከሚኖሩ ዜጎች ግብር መሰብሰብ ነዉ»

This browser does not support the audio element.

 የሆላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሀልቤ ዜሌስትራ፤ ባወጡት መግለጫ እንዳመለከቱት ዉሳኔው የተላለፈው በሀገራቸው የሚኖሩ ኤርትራውያን ለኤርትራ መንግሥት ግብር እንዲከፍሉ የማስገደድ እና የማስፈራራት ተግባር የሚፈጸምባቸው በመሆኑ እና፤ ይህ እንዳይደረግም ኔዘርላንድስ በተደጋጋሚ ያቀረበችው ጥያቄ ተግባራዊ ባለመሆኑ እንደወነ አመልክተዋል። ከብራስልስ ገበያው ንጉሤ ዘገባ ልኮልናል።

ገበያው ንጉሤ

ሸዋዬ ለገሠ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW