ንፋስ የሚያዛምተዉ በሽታ
ማክሰኞ፣ መጋቢት 20 2003ማስታወቂያ
ህክምናዉን በአግባቡና በጥንቃቄ ያልተከታተለና ያልታከመ አንድ ሰዉ በዓመት ከአስር እስከ አስራ አምስት የሚሆኑ ሰዎችን በዚህ በሽታ ሊያስይዝ እንደሚችል ጥናቶች ያመለክታሉ። በተለይ አሁን ዓለም ያሳሰበዉ የሳንባ ነቀርሳ መድሃኒት የተላመደዉ ዓይነት ነዉ። በዚህ የጤና ችግር 27 ሀገራት ክፉኛ ተጠቅተዋል። የኢትዮጵያ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የሳንባ ነቀርሳና የተላላፊ በሽታዎች ዘርፍ አስተባባሪ እንደሚሉት ኢትዮጵያ ባለፈዉ ከነበረችበት አስራ አምስተኛ ደረጃ ዘንድሮ ወደአስራ ስድስት ወርዳለች።
ሸዋዬ ለገሠ
ተክሌ የኋላ