አምስት ፓርቲዎች ሊዋሐዱ ነው
ሰኞ፣ ግንቦት 5 2011ማስታወቂያ
አምስት ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሊዋሐዱ መሆኑን አስታወቁ። በመጪው ሐሙስ ይፈፀማል በተባለው ውሕደት ኅብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እንደሚቋቋም በዛሬው ዕለት ይፋ አድርገዋል። ተዋሕደናል ያሉት ቱሳ የኢትዮጵያ ትንሣኤ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የሽግግር ምክር ቤት፣ ኢትዮጵያችን ሕዝባዊ ንቅናቄ፣ የኦሞ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ኅብረት እና ደቡብ ኢትዮጵያ አረንጓዴ ኮከቦች ቅንጅት ናቸው። አቶ ተሻለ ሰብሮ የሚመሩት የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ በውኅደቱ ተስማምቶ ሒደቱን ቢጀምርም በስተመጨረሻ አፈንግጧል።
ጌታቸው ተድላ ኃይለጊዮርጊስ
ኂሩት መለሰ