1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

አምንስቲ ኢንተርናሽናል በትግራይ የሰላማዊ ሰዎች ደህንነት ይጠበቅ አለ

ማክሰኞ፣ ኅዳር 15 2013

የኢትዮጵያ የፌዴራል መንግስት እና   የህወሓት ኃይሎች እያደረጉ ባለው ጦርነት  ጦርነት የሰላማዊ ሰዎች ደህንነት ሊጠብቁ እንደሚገባ ዓለማቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት አምንስቲ ኢንተርናሽናል አሳሰበ። ሁለቱም ኃይሎች ከልክ ያለፈ ኃይል የሚጠቀሙ ከሆኑ  በጦር ወንጀለኝነት ሊያስጠይቃቸው  እንደሚችል በአምንስቲ ኢንተርናሽናል አስታውቋል።

Logo von Amnesty International

የአምንስቲ ኢንተርናሽናል ማሳሰቢያ

This browser does not support the audio element.

የኢትዮጵያ የፌዴራል መንግስት እና   የህወሓት ኃይሎች እያደረጉ ባለው ጦርነት  ጦርነት የሰላማዊ ሰዎች ደህንነት ሊጠብቁ እንደሚገባ ዓለማቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት አምንስቲ ኢንተርናሽናል አሳሰበ። አምንስቲ ትናንት ባወጣው መግለጫው እንዳመለከተው በሁለቱ ወገኖች መካከል እየተደረገ ያለው ጦርነት መቀሌ ከተማ መጠጋቱን ተከትሎ የሰላማዊ ሰዎች ደህንነት ከምንግዜውም በላይ እንደሚያሳስበው አስታውቋል። ሁለቱም ኃይሎች ከልክ ያለፈ ኃይል የሚጠቀሙ ከሆኑ  በጦር ወንጀለኝነት ሊያስጠይቃቸው  እንደሚችል በአምንስቲ ኢንተርናሽናል የአፍሪቃ ቀንድ ጉዳዮች አጥኚ አቶ ፍሰሃ ተክሌ ተናግረዋል።

ታምራት ዲንሳ

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW