1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ
ሳይንስኢትዮጵያ

አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ እና አፍሪካ፦ አንድ ለአንድ ከአስመላሽ ተካ ጋር

ዓርብ፣ ግንቦት 22 2017

አስመላሽ ተካ ለኢትዮጵያ ቋንቋዎች የማሽን ትርጉም አገልግሎት የሚያቀርበው ልሳን ኩባንያ ተባባሪ መሥራች ነው። መቀመጫውን በርሊን ያደረገው ልሳን በሥራው ከአርቴፊሺያል ኢንተለጀንስ ጋር በጥብቅ ይተሳሰራል። አስመላሽ የአንድ ለአንድ እንግዳ ነው። አሜሪካ እና ቻይና ስለሚወዳደሩበት ቴክኖሎጂ እና ለአፍሪካ ስለሚኖረው ፋይዳ እሸቴ በቀለ አነጋግሮታል።

የልሳን ኩባንያ ተባባሪ መሥራች አስመላሽ ተካ
አስመላሽ ተካ ለኢትዮጵያ ቋንቋዎች የማሽን ትርጉም አገልግሎት የሚያቀርበው ልሳን ኩባንያ ተባባሪ መሥራች ነው።ምስል፦ Ayse Tasci/DW

አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ እና አፍሪካ፦ አንድ ለአንድ ከአስመላሽ ተካ ጋር

This browser does not support the audio element.

ዩናይትድ ስቴትስ እና ቻይና ብርቱ ውድድር የገጠሙበት አርቴፊሺያል ኢንተለጀንስ አንዳንዶች ለአፍሪካ ከፍ ያለ ጠቀሜታ ይዞ እንደመጣ ያምናሉ። ከ1.5 ቢሊዮ በላይ ነዋሪዎች ያሏት አኅጉር በናጠጡት ሀገሮች ለሚሰሩ የአርቴፊሺያል ኢንተለጀንስ ውጤቶች ገበያ ከመሆን የዘለለ ሚና ሊኖራት ስለመቻሉ ጥርጣሬ ያላቸውም አይጠፉም። 

አስመላሽ ተካ ግን ትምህርት እና ጤናን የመሳሰሉ ዘርፎችን ጨምሮ አርቴፊሺያል ኢንተለጀንስ በተለያዩ መስኮች ለአፍሪካ ጥቅም እንደሚኖረው ያምናል። ለዚህም ራሱ አስመላሽ ያቋቋመው ልሳን የተባለ ኩባንያ ኹነኛ ምሳሌ ነው።

ልሳን ለኢትዮጵያ ቋንቋዎች የማሽን የትርጉም አገልግሎት ያቀርባል። በአሁኑ ወቅት ለእንግሊዘኛ፣ አማርኛ እና ትግርኛ የትርጉም አገልግሎት የሚሰጠው ልሳን ወደ ፊት አፋን ኦሮሞ እና ሶማሊኛን ጨምሮ ሌሎች ቋንቋዎች የማካተት ዕቅድ እንዳለው አስመላሽ ለዶይቼ ቬለ አስረድቷል። ልሳን ከትርጉም በተጨማሪ ድምጽ ወደ ጽሁፍ የሚቀይር በአርቴፊሺያል ኢንተለጀንስ ላይ የተመሠረተ አገልግሎት በማበልጸግ ላይ ይገኛል። 

ልሳን የተሰማራበት ሥራ ጉግል እና ፌስቡክን የመሳሰሉ ኩባንያዎች በአርቴፊሺያል ኢንተለጀንስ አማካኝነት አገልግሎት የሚሰጡበት ነው። ይሁንና ቴክኖሎጂውን ለማበልጸግ ልሳን የሚከተለው መንገድ እና የእነ ጉግል አካሔድ የተለያየ ነው። 

በዚህ ቃለ-መጠይቅ ስለ አርቴፊሺያል ኢንተለጀንስ ተስፋ እና ሥጋት፣ በቴክኖሎጂው ግንባታ ውስጥ አፍሪካ ስለሚኖራት ሚና አስመላሽ ተካ አስተያየቱን ሰጥቷል። 

ቃለ- መጠይቁን ለማድመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ 

አርታዒ ታምራት ዲንሳ  
 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW