1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አስደማሚ ርብርብ በምሽት የባሕር ላይ ስደተኞችን ለማዳን

01:54

This browser does not support the video element.

ረቡዕ፣ መጋቢት 11 2016

እጅግ አስደማሚ በሆነ የምሽት ሕይወት አድን ርብርብ 75 የባሕር ላይ ስደተኞች ሰጥመው ከመሞት ተርፈዋል ። ሰሜናዊ የአፍሪቃ አቅጣ በዓለም አቀፍ የባሕር ወሰን የሜዲቴራኒያ ባሕር ላይ ስደተኞቹን ከመስጠም የታደጉት አትራፊ ያልሆነ የመርከብ ተቋም ሕይወት አድን ሠራተኞች ናቸው

እጅግ አስደማሚ በሆነ የምሽት ሕይወት አድን ርብርብ 75 የባሕር ላይ ስደተኞች ሰጥመው ከመሞት ተርፈዋል ። ሰሜናዊ የአፍሪቃ አቅጣ በዓለም አቀፍ የባሕር ወሰን የሜዲቴራኒያ ባሕር ላይ ስደተኞቹን ከመስጠም የታደጉት አትራፊ ያልሆነ የመርከብ ተቋም ሕይወት አድን ሠራተኞች ናቸው ። የስደተኞቹ ጀልባ ስትገለበጥ 45 ሰዎች ውኃ ውስጥ ቢገቡም የሕይወት አድን አልባሳትን በማደል ከመስጠም ታድገዋቸዋል ። እሁድ ምሽት በተደረገው የሕይወት አድን ርብርብ እንደ ዕድል የሰጠመ የለም ። ሆኖም እንደ ዓለም አቀፍ ተቋማት መረጃ ባለፈው የጎርጎሪዮስ ዓመት ብቻ 2,500 ስደተኞች ሰጥመዋል ወይ ተሰውረዋል ። ባለፉት ሰባት ወራት ደግሞ 226 ሰዎች የደረሱበት ዐይታወቅም ።

የቪዲዮ ዘገባ፦ ዶይቸ ቬለ
ምንጭ አሶሺየትድ ፕሬስ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW