1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሶማሊያ መሪዎች ውዝግብ 

ሐሙስ፣ መስከረም 6 2014

የሶማሊያ መንግሥት የደኅንነት ቢሮ ሰራተኛ ከታገቱ በኋላ ተገድለው መገኘታቸው ያስነሳው ሌላ  ውዝግብ ትኩረት ስቧል። ክራይስ ግሩፕ የተባለው ድርጅት እንዳለው የደኅንነት ሠራተኛዋ ግድያ ከሶማሊያ ወታደሮች የውጭ ስልጠና ጋር በተያያዘ የሚያውቁትን መረጃ እንዳያወጡ ለማድረግ የተፈጸመ ሳይሆን እንዳልቀረ አስታውቋል።

Somalia Präsident Mohamed Abdullahi Mohamed | Farmajo
ምስል Str/AFP

የሶማሊያ መሪዎች ውዝግብ 

This browser does not support the audio element.

በሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሞሐመድ አብዱላሂና በጠቅላይ ሚኒስትር ሞሐመድ ሁሴን ሮብሌ መካከል የተፈጠረው ውዝግብ በችግር ላይ ያለችው ሀገር ጭርሱን ወደ ባሰ የርስ በርስ ግጭት እንዳትገባ አስግቷል።  በተለይ የሶማሊያ መንግሥት የደኅንነት ቢሮ ሰራተኛ ከታገቱ በኋላ ተገድለው መገኘታቸው ያስነሳው ሌላ  ውዝግብ ትኩረት ስቧል።የግጭቶችን መንስኤና ሂደት በማጥናት መፍትሄውን የሚጠቁመው ክራይስ ግሩፕ የተባለው ድርጅት እንዳለው የደኅንነት ሠራተኛዋ ግድያ ከሶማሊያ ወታደሮች የውጭ ስልጠና ጋር በተያያዘ የሚያውቁትን መረጃ እንዳያወጡ ለማድረግ የተፈጸመ ሳይሆን እንዳልቀረ አስታውቋል። በግድያው አሸባብ ቢጠረጠርም አሸባብ ግን ውንጀላውን አስተባብሏል። ዛሬ እንደተሰማው ፕሬዝዳንቱ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ሥልጣን በከፊል ገድበዋል።

 


ገበያው ንጉሴ


ኂሩት መለሰ
እሸቴ በቀለ
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW